የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፈረንሳይ ሊዮን የበረራ አገልግሎት አፍሪካን ከዓለም ለማገናኘት በሚደረገው ጉዞ ቁልፍ ምዕራፍ ነው

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

‎አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):-‎የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፈረንሳይ ሊዮን የበረራ አገልግሎት አፍሪካን ከዓለም ለማገናኘት በሚደረገው ጉዞ በቁልፍ ምዕራፍነት እንደሚወሰድ የአየር መንገድ ግሩፑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ገለጹ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንሳይ ሊዮን አዲስ የመንገደኞች በረራ አገልግሎትን አስጀምሯል።


የአየር መንገድ ግሩፑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት፤ የፈረንሳይ የኢኮኖሚ፣ የባህልና የፈጠራ ብልፅግና ማዕከሏ ሊዮን የሚደረገው በረራ የተደራሽነት አድማስን ያሰፋል ብለዋል።

ወደ ሊዮን ከተማ የሚደርገው በረራም የአውሮፓ መዳረሻውን ወደ 23ኛ በማሳደግ የፈረንሳይ ከተሞች ከአፍሪካ ጋር በማገናኘት ስኬታማ ሥራ እየተሰራ መሆኑን እንደሚያሳይ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንድ በፈረንሳይና የአውሮፓ ከተሞች የሚያደርገው የበረራ አገልግሎትም የኢትዮ-አውሮፓን ግንኙነት በማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል።


አየር መንገዱ ለደንበኞቹ በሚያቀርባቸው ጥራትና ብቃት ያላቸው የበረራ አገልግሎቶችም ዓለም አቀፍ የአቭዬሽን ኢንዱስትሪ ስመጥሩነቱን በተግባር እያስመሰከረ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በሚቀጥለው በጀት ዓመትም አምስት አዳዲስ የበረራ አገልግሎትን በማስጀመር ኢትዮጵያና አፍሪካን በዓለም የንግድ፣ ቱሪዝምና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የማስተሳሰር ሚናውን እንደሚወጣ አረጋግጠዋል።

አየር መንገዱ የበረራ አገልግሎት ጥራትን ለማላቅም ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በላቀ ቴክኖሎጂዎችና በደንበኛ ተኮር አገልግሎት ላይ ሰፊ ኢንቨስትመንት እያደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ለሚደረገው የበረራ አገልግሎት መሳካት ድጋፍና ትብብር ላደረጉ ባለድርሻ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።


በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲስ ላሜክ በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ያስጀመረው የበረራ አገልግሎት የሀገራቱን ሁለንተናዊ ግንኙነት ለማጠናከር ጉልህ ፋይዳ አለው ብለዋል።

በተለይም የኢትዮ-ፈረንሳይን ጠንካራ የዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት በህዝብ ለህዝብ ትስስር፣ በንግድና ኢንቨስትመንት ለማጠናከር እንደሚረዳ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026