የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የእርሻ ስራን በግብርና ባለሙያ በመታገዝ በማከናወናችን ምርታማነታችን አድጓል-የጉራጌ ዞን አርሶ አደሮች

Jul 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):- የመኸር ወቅት የእርሻ ስራን በግብርና ባለሙያዎች በመታገዝ እያከናወኑ በመሆኑ ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱን የጉራጌ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ አርሶ አደሮች ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በግብርና ባለሙያዎች እየተደረገላቸው ያለው ድጋፍ የተቀናጀ የግብርና ስነ-ዘዴን በመጠቀም በእንስሳት እርባታም ጭምር ውጤታማ ሆነዋል።

የእርሻ ስራን በግብርና ባለሙያዎች በመታገዝ እያከናወኑ በመሆኑ ምርታማነታቸው እያደገ መምጣቱንም አርሶ አደሮቹ ገልጸዋል።

የአበሽጌ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር ሰብስቤ ወልደሃዋርያት፤ አሁን ላይ ለዘር ምቹ ወቅት በመሆኑ በግብርና ባለሙያዎች ታግዘው የግብርና ልማት ሥራቸውን እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህም እስካሁን ሁለት ሄክታር መሬታቸውን በበቆሎ ዘር መሸፈናቸውንና አንድ ሄክታሩን ደግሞ በጤፍ ለመሸፈን መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ የጌታ ወረዳ አርሶ አደር ጀማል ሟናጋ በበኩላቸው፤ ድንችን በአንድ ሄክታር መሬት ላይ ተክለው በመንከባከባቸው ለምግብ ፍጆታ የሚውል ምርት ከማምረት ባለፈ ለገበያ ጭምር በማውጣት ትርፋማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት ቀሪ አንድ ሄክታር ከግማሽ መሬታቸውን አርሰው በማለስለስ ሰብል ለመዝራት መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።

የሚደረግላቸው ሙያዊ ድጋፍ ምርታማነታቸውን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የተሳካ ስራ እንዲሰሩ ምክንያት እንደሆነ የገለፁት ደግሞ አርሶ አደር ገብሬ ዛጋ ናቸው።

የተቀናጀ የግብርና አሰራርን በመከተል የተለያዩ ሰብሎችን በማልማትና እንስሳትን በማርባት ተግባር ላይ መሰማራታቸው የተሻለ ኑሮ እንዲመሩ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

ዘንድሮም ካላቸው የእርሻ መሬት ላይ አንድ ሄክታር መሬት በገብስ ለመሸፈን መዘጋጀታቸውን ጠቅሰው ለዚህም የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር እንደቀረበላቸው ተናግረዋል።


የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ፤ በዞኑ በተያዘው መኸር ከ43 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በበቆሎ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል።

በመኸር እርሻ 180 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት መታረሱን ገልፀው እስካሁን 160 ሺህ የሚጠጋ ማሳ መልማቱን አስረድተዋል።

የግብርና ሜካናይዜሽንን በማጠናከር የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማላቅ እየተሰራ ያለው ስራ የዘርፉን ውጤታማነት እያሳደገው መሆኑንም አቶ አበራ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026