የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በተያዘው ክረምት በ100 ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ በኩታ ገጠም ይተከላል

Jul 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን በተያዘው ክረምት በ100 ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ በኩታ ገጠም እንደሚተከል የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የአትክልትና ፍራፍሬ ባለሙያ አቶ ተሾመ በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለቡና ልማት ስራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

በዞኑ በያዝነው ክረምት በቡና ከሚለማው አጠቃላይ ከ320 ሄክታር መሬት ውስጥ ከ100 ሄክታር በላይ የሚሆነው መሬት በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በበጋው ወቅት ከተዘጋጀው ከ916 ሺህ በላይ የቡና ችግኝ ውስጥም ከ330 ሺህ በላይ የሚሆነው ለኩታ ገጠም ልማት እንደሚውል ተናግረዋል።

የቡና ኩታ ገጠም ልማቱ የሚካሄደውም ተስማሚ ስነ ምህዳርና የአየር ንብረት ባላቸው በደብረ ኤሊያስ፣ በማቻከልና ጎዛምን ወረዳዎች መሆኑን አመላክተዋል።


በዞኑ በሚካሄደው የቡና ልማትም ከ690 በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

በዞኑ የጎዛምን ወረዳ የሊባኖስ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ክብረት በዛበህ ፤ በተያዘው ዓመት ቡናን በኩታ ገጠም መትከል መጀመራቸውን ነው የሚናገሩት።

ከዚህ በፊት ቡናን በጓሯቸው በማልማት ለቤት ውስጥ ፍጆታ ይጠቀሙ እንደነበር አስታውሰው በአሁኑ ወቅም ከግማሽ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ላይ ቡናን በኩታገጠም በማልማት ለገበያ ለማቅረብ እየሰራሁ ነው ብለዋል።

የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መንግስቱ ክፍሌ በበኩላቸው እንደሌሎች ሰብሎች ቡናን በኩታ ገጠም ለማልማት ከግማሽ ሄክታር በላይ መሬት በማዘጋጀት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም የማሳ ዝግጅት በማጠናቀቅ በጋራ የሚተከልበትን ቀን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026