የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በተያዘው ክረምት በ100 ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ በኩታ ገጠም ይተከላል

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን በተያዘው ክረምት በ100 ሄክታር መሬት ላይ የቡና ችግኝ በኩታ ገጠም እንደሚተከል የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የአትክልትና ፍራፍሬ ባለሙያ አቶ ተሾመ በላይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለቡና ልማት ስራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

በዞኑ በያዝነው ክረምት በቡና ከሚለማው አጠቃላይ ከ320 ሄክታር መሬት ውስጥ ከ100 ሄክታር በላይ የሚሆነው መሬት በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በበጋው ወቅት ከተዘጋጀው ከ916 ሺህ በላይ የቡና ችግኝ ውስጥም ከ330 ሺህ በላይ የሚሆነው ለኩታ ገጠም ልማት እንደሚውል ተናግረዋል።

የቡና ኩታ ገጠም ልማቱ የሚካሄደውም ተስማሚ ስነ ምህዳርና የአየር ንብረት ባላቸው በደብረ ኤሊያስ፣ በማቻከልና ጎዛምን ወረዳዎች መሆኑን አመላክተዋል።


በዞኑ በሚካሄደው የቡና ልማትም ከ690 በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

በዞኑ የጎዛምን ወረዳ የሊባኖስ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ክብረት በዛበህ ፤ በተያዘው ዓመት ቡናን በኩታ ገጠም መትከል መጀመራቸውን ነው የሚናገሩት።

ከዚህ በፊት ቡናን በጓሯቸው በማልማት ለቤት ውስጥ ፍጆታ ይጠቀሙ እንደነበር አስታውሰው በአሁኑ ወቅም ከግማሽ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ላይ ቡናን በኩታገጠም በማልማት ለገበያ ለማቅረብ እየሰራሁ ነው ብለዋል።

የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር መንግስቱ ክፍሌ በበኩላቸው እንደሌሎች ሰብሎች ቡናን በኩታ ገጠም ለማልማት ከግማሽ ሄክታር በላይ መሬት በማዘጋጀት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅትም የማሳ ዝግጅት በማጠናቀቅ በጋራ የሚተከልበትን ቀን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026