የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ገጽታንም በእጅጉ የለወጡ ናቸው

Jul 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጡና ገጽታን በእጅጉ የለወጡ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡

ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚ እና በፖለቲካ የተመዘገቡ ስኬቶችን አስመልክቶ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በቆይታቸውም ባለፉት ዓመታት አዲስ አበባን የለወጡ እጅግ አስደማሚ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባል አለማየሁ አረዳ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተከናወኑት የልማት ሥራዎች እጅግ ስኬታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ከተማዋን ወደ ላቀ ደረጃ የለወጡና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም በአስፈጻሚው አካልና በምክር ቤቱ መካከል የነበረው ግንኙነት እጅግ ጤናማና መልካም የሥራ ባህል የነበረው መሆኑን አብራርተዋል።

ይህ አዎንታዊ አሠራርና መልካም ባህል በቀጣዩ ምክር ቤትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን ትልቅ ተስፋ ገልጸዋል።


ሌላኛዋ የምክር ቤት አባል ደብረሲና ሙሴ በበኩላቸው ያለፉት አምስት ዓመታት ለምክር ቤቱ አዲስ የሥራ ምዕራፍና ስኬት የታየበት ወቅት እንደነበር ገልጸዋል።

በዚህ ጊዜ ውስጥ የተከናወኑት የማህበራዊ ዘርፍ ሥራዎች በግልጽ በአይን የሚታዩና የሕዝብን የኑሮ ፍላጎት በአግባቡ የመለሱ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ነባር የጤና ተቋማት እንዲስፋፉና አዳዲስ ዘመናዊ ተቋማት እንዲገነቡ መደረጉ እንዲሁም፤ የትምህርት ተደራሽነትና የተማሪዎች ቅበላ እንዲጨምር ምክር ቤቱ ጠንካራ ግፊት ሲያደርግ መቆየቱንና አስፈጻሚው አካልም በዚህ ልክ የተሻሉ ሥራዎችን ማከናወኑን ጠቅሰዋል።

ምክር ቤቱ የሕዝብ ድምፅ በመሆን ለነዚህ መልካም ሥራዎች ጠንካራ መሠረት መጣሉን የገለጹት አባልዋ ቀጣዩ ምክር ቤትም የተጀመረውን የልማት ጉዞ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።


የምክር ቤት አባሉ ኢቲሳ ደሜ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ያለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ፈጣን ለውጥ የታየበት ወቅት እንደነበር ገልጸዋል።

በጤናው ዘርፍም ዘመናዊ ማሽነሪዎች የተሟሉላቸው ሆስፒታሎች መገንባታቸው ቀድሞ ወደ ውጭ አገር የሚደረጉ የሕክምና ጉዞዎችን እንደሚያስቀርና በትምህርትም ዘርፍ የተማሪዎች ውጤት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸዋል።

የተጀመሩት አበረታች የልማትና የፖለቲካ ስኬቶች ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመሆኑም የሚቀጥለው ምክር ቤት የተጀመሩትን ፈጣን የልማት ሥራዎች በቁርጠኝነት ይዞ መስራትና ህብረተሰቡን በታማኝነት ማገልገል እንዳለበት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።


የምክር ቤት አባሉ አባወይ ዮሐንስ እንደገለጹት ባለፉት አመታት ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹና ተወዳዳሪ ከማድረግ አንፃር ማህበረሰቡን መሰረት ያደረጉና የልማት ጥያቄዎችን በተግባር የመለሱ ሰፋፊ ፕሮጀክቶች ተተግብረዋል።

ነዋሪዎች ቀድሞ ሩቅ ቦታ ሄደው የሚያዩትንና የሚመኙትን ዘመናዊ የከተማ አኗኗር፣ በአካባቢያቸው ማግኘት መቻላቸው የፕሮጀክቶቹን የሕዝብ ተጠቃሚነት ማረጋገጫ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም በጤና እና በትምህርት ዘርፍ አበረታች ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በበጀት ዓመቱ 47 አዳዲስ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደሥራ ገብተዋል

ሐረር፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 47 አዳዲስ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን የክልሉ ኢን...

Jul 16, 2026

የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ የሕዝቡን የተዳፈነ የዘመናት የልማት ጥያቄ የመለሰ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የደብረ ማርቆስ ንጉሥተክለሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ የሕዝቡን የተዳፈነ የዘመናት የልማት ጥያቄ የመለሰ ነው ሲሉ የ...

Jul 14, 2026

በአማራ ክልል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ተሰራጭቷል

ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መ...

Jul 11, 2026

በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ ይቀጥላል

ደሴ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ ቴክኖሎጂንና አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ እ...

Jul 10, 2026