🔇Unmute
ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ለዘንድሮው የመኸር ሰብል ልማት ስምንት ነጥብ ስድስት ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል።
እስካሁን ባለው ሒደትም ከአምስት ነጥብ አራት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ወደ አካባቢው የገባ ሲሆን ከዚህ ውስጥም አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የሚሆነውን ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል።

የማዳበሪያ ስርጭቱ ቀድመው ለሚዘሩ እንዲሁም በክረምት ለተሽከርካሪ አስቸጋሪ ለሆኑ አካባቢዎች ቅድሚያ በመስጠት የተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።
ማዳበሪያንና ሌሎች ግብአቶችን በወቅቱ ተደራሽ በማድረግ የክልሉን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ሰፊ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም ነው ያስረዱቱ።
የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ደመቀ አድማሱ በበኩላቸው፣ በዞኑ ለዘንድሮው መኸር እርሻ ለማቅረብ ከታቀደው 644 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 517 ሺህ ኩንታሉን ማስገባት ተችሏል።

ከዚህ ውስጥም 387 ሺህ ኩንታል የሚሆነውን ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል።
በሰሜን ወሎ ዞን ለመኸር ምርቱ ለማቅረብ ከታቀደው 217 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውሰጥ 160 ሺህ ኩንታሉን ለአርሶ አደሩ ማሰራጨት ተችሏል ያሉት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ተገኝ አባተ ናቸው።

በምርት ዘመኑ በተሻሻሉ ዘመናዊ አሰራሮች 231 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ 7 ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ እንዲቻል ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መ...
Jul 11, 2026
ደሴ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ ቴክኖሎጂንና አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ እ...
Jul 10, 2026
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026