🔇Unmute
አዳማ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምን በማስፈን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ውጤታማ ለማድረግ ያስቻሉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ ገለጹ።
የክልሉ 2018 ዓ.ም የመንግሥትና የፓርቲ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአዳማ አባገዳ አዳራሽ እንደቀጠለ ነው፡፡
የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንትአቶ አወሉ አብዲ መግለጫ ሰጥተዋል።
በበጀት ዓመቱ በተለይም በክልሉ ሰላምና ጸጥታን በማጠናከር ረገድ ውጤታማ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ በተለያየ መልኩ የፀረ-ሰላም ኃይሎች የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማደናቀፍ ቢሞክሩም ሕዝቡና የክልሉ የጸጥታ ኃይል በጋራ ሆነው ለሰላም መስፈን በሠሩት ሥራ የልማት ሥራዎችን ማስቀጠል ተችሏል ብለዋል።
በሰፈነው ሰላም የልማት ስራዎችን በተሳካ ሁኔታ ማስቀጠል መቻሉን ተናግረው አሁንም የተገኘውን ሰላም ለማጽናት ጠንካራ የጸጥታ ኃይል የመገንባቱ ሥራ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።
በክልሉ በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎችም በተለይ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ውጤታማ ከማድረግና የክልሉን ገቢ ከማሳደግ አንጻር ውጤት መገኘቱንም አመልክተዋል።
እንደ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ በ2012 ዓ.ም 70 ቢሊዮን ብር የነበረውን የክልሉን ገቢ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 341 ቢሊዮን ብር ማድረስ ተችሏል።
በዚህም ለክልሉ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ሥራዎች የሚያስፈልገውን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን አቅም እየተገነባ መሆኑን አስረድተዋል።
በተመሳሳይ በ'ቡሳ ጎኖፋ' ሥርዓት አማካኝነት የኦሮሞ ሕዝብ የቀደመ የመረዳዳት ባህልን እንዲያጠናክር በማድረግ ችግሮችን በራስ አቅም ተደጋግፎ ለማለፍ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በበጎ ፈቃድ አገልግሎትም በተለይ በአረንጓዴ አሻራ፣ አቅመ ደካሞችን በማገዝ እና በሌሎች መንገዶች አብሮነትን ያጠናከሩ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።
በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋለውን ሌብነት፣ የሥነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሠራር ለማስቀረት የመንግሥት አገልግሎትን ለማሻሻልና ለማዘመን መሰራቱን ገልጸው፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።
በመጀመሪያው ዙር አምስት የክልል ከተሞች ላይ የተጀመረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ በሁለተኛው ዙር 26 ከተሞችን ጨምሮ በአሁኑ ወቅት በ96 ከተሞች ላይ መስፋፋቱን አንስተዋል።
ሐረር፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 47 አዳዲስ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን የክልሉ ኢን...
Jul 16, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የደብረ ማርቆስ ንጉሥተክለሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ የሕዝቡን የተዳፈነ የዘመናት የልማት ጥያቄ የመለሰ ነው ሲሉ የ...
Jul 14, 2026
ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መ...
Jul 11, 2026
ደሴ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ ቴክኖሎጂንና አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ እ...
Jul 10, 2026