🔇Unmute
አዳማ፤ ሐምሌ 8/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምን በማስፈን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ውጤታማ ለማድረግ ያስቻሉ ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አወሉ አብዲ ገለጹ።
የክልሉ 2018 ዓ.ም የመንግሥትና የፓርቲ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአዳማ አባገዳ አዳራሽ እንደቀጠለ ነው፡፡
የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንትአቶ አወሉ አብዲ መግለጫ ሰጥተዋል።
በበጀት ዓመቱ በተለይም በክልሉ ሰላምና ጸጥታን በማጠናከር ረገድ ውጤታማ ሥራ መሠራቱን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ በተለያየ መልኩ የፀረ-ሰላም ኃይሎች የሰላምና ልማት ሥራዎችን ለማደናቀፍ ቢሞክሩም ሕዝቡና የክልሉ የጸጥታ ኃይል በጋራ ሆነው ለሰላም መስፈን በሠሩት ሥራ የልማት ሥራዎችን ማስቀጠል ተችሏል ብለዋል።
በሰፈነው ሰላም የልማት ስራዎችን በተሳካ ሁኔታ ማስቀጠል መቻሉን ተናግረው አሁንም የተገኘውን ሰላም ለማጽናት ጠንካራ የጸጥታ ኃይል የመገንባቱ ሥራ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።
በክልሉ በማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎችም በተለይ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ውጤታማ ከማድረግና የክልሉን ገቢ ከማሳደግ አንጻር ውጤት መገኘቱንም አመልክተዋል።
እንደ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ በ2012 ዓ.ም 70 ቢሊዮን ብር የነበረውን የክልሉን ገቢ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 341 ቢሊዮን ብር ማድረስ ተችሏል።
በዚህም ለክልሉ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ሥራዎች የሚያስፈልገውን ወጪ በራስ አቅም ለመሸፈን አቅም እየተገነባ መሆኑን አስረድተዋል።
በተመሳሳይ በ'ቡሳ ጎኖፋ' ሥርዓት አማካኝነት የኦሮሞ ሕዝብ የቀደመ የመረዳዳት ባህልን እንዲያጠናክር በማድረግ ችግሮችን በራስ አቅም ተደጋግፎ ለማለፍ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በበጎ ፈቃድ አገልግሎትም በተለይ በአረንጓዴ አሻራ፣ አቅመ ደካሞችን በማገዝ እና በሌሎች መንገዶች አብሮነትን ያጠናከሩ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።
በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋለውን ሌብነት፣ የሥነ ምግባር ጉድለትና ብልሹ አሠራር ለማስቀረት የመንግሥት አገልግሎትን ለማሻሻልና ለማዘመን መሰራቱን ገልጸው፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።
በመጀመሪያው ዙር አምስት የክልል ከተሞች ላይ የተጀመረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ በሁለተኛው ዙር 26 ከተሞችን ጨምሮ በአሁኑ ወቅት በ96 ከተሞች ላይ መስፋፋቱን አንስተዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026