🔇Unmute
ደሴ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦በከተማ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ገለፁ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሰላምን ከማጽናት ባሻገር ሰፋፊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ተችሏል።
በዚሁ ወቅት ከተከናወኑት የልማት ስራዎች መካከል የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የአምስት ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ ተጠቃሽ መሆኑን አመልክተዋል።
በተጨማሪም የትምህርትና የጤና ተቋማትን ደረጃ የማሻሻል እና ሌሎች የማሕበረሰቡን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ተናግረዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎንም የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ተችሏል ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው፣ የልማት ስራው በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በ2019 በጀት ዓመት በተለይ ለመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ ለኮሪደር ልማት፣ ገበያን ማረጋጋት፣ ለሥራ እድል ፈጠራና ሌሎችም ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ነው የተናገሩት።

የደሴ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ሸህ መሀመድ ሰይድ፣ በከተማ አስተዳደሩ በተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተለይ በአስፋልት መንገድ ግንባታ፣ በኮሪደር ልማት፣ በገበያ ማረጋጋትና በሌሎችም የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ አያል ሰይድ በሰጡት አስተያየት፣ የከተማ አስተዳደሩ ነዋሪውን በማስተባበር ሰላም በማጽናት፣ በልማት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።
ሐረር፤ ሐምሌ 7/2018 (ኢዜአ)፡-በሐረሪ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 47 አዳዲስ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ መግባታቸውን የክልሉ ኢን...
Jul 16, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የደብረ ማርቆስ ንጉሥተክለሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ የሕዝቡን የተዳፈነ የዘመናት የልማት ጥያቄ የመለሰ ነው ሲሉ የ...
Jul 14, 2026
ደሴ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ለመጪው መኸር ሰብል ልማት የሚውል ከአራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መ...
Jul 11, 2026
ደሴ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ወሎ ዞን በግብርናው ዘርፍ ቴክኖሎጂንና አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የተገኘው አበረታች ውጤት ተጠናክሮ እ...
Jul 10, 2026