የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከተማ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ስራዎች ስኬታማ ናቸው

Jul 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦በከተማ አስተዳደሩ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተግባራዊ የተደረጉ የልማት ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ገለፁ።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ እንደገለጹት፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሰላምን ከማጽናት ባሻገር ሰፋፊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ተችሏል።

በዚሁ ወቅት ከተከናወኑት የልማት ስራዎች መካከል የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የአምስት ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ ተጠቃሽ መሆኑን አመልክተዋል።

በተጨማሪም የትምህርትና የጤና ተቋማትን ደረጃ የማሻሻል እና ሌሎች የማሕበረሰቡን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ስራዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ተናግረዋል።

ከዚሁ ጎን ለጎንም የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ተችሏል ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው፣ የልማት ስራው በአዲሱ በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በ2019 በጀት ዓመት በተለይ ለመኖሪያ ቤት ግንባታ፣ ለኮሪደር ልማት፣ ገበያን ማረጋጋት፣ ለሥራ እድል ፈጠራና ሌሎችም ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ነው የተናገሩት።


የደሴ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ሸህ መሀመድ ሰይድ፣ በከተማ አስተዳደሩ በተከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይ በአስፋልት መንገድ ግንባታ፣ በኮሪደር ልማት፣ በገበያ ማረጋጋትና በሌሎችም የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።


የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሮ አያል ሰይድ በሰጡት አስተያየት፣ የከተማ አስተዳደሩ ነዋሪውን በማስተባበር ሰላም በማጽናት፣ በልማት ተጠቃሚ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026