🔇Unmute
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በማሕበራዊ እና ኢኮኖሚ መስኮች ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
የክልሉ ምክር ቤት 5ኛ የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤ የ2018 በጀት ዓመት የልማትና የመልካም አስተዳደር አፈጻጸም ሪፖርትን አዳምጧል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ሪፖርቱን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ የነበሩ ፈተናዎችን በመቋቋም በግብርና፣ በማዕድን፣ በትምህርትና በሌሎችም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች አበረታች ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል።
ከዚህ ውስጥም በ2017/18 የምርት ዘመን በመኸርና በበጋ መስኖ ልማት 229 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ አትክልትና ፍራፍሬን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎችን ማልማት መቻሉን ገልጸዋል።
በቡና ልማት ዘርፍም በአርሶ አደሮችና በባለሀብቶች ከለማው 73 ሺህ 425 ሄክታር መሬት 53 ሺህ 756 ቶን ምርት መገኘቱን አብራርተዋል።
በበጀት ዓመቱ በማዕድን ልማት ዘርፍ 6 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ለማድረግ ታቅዶ 7 ሺህ 098 ኪሎ ግራም ወርቅ ለማቅረብ መቻሉን ገልጸው አፈጻጸሙም ከእቅድ በላይ ነው ብለዋል።
የትምህርት ፍትሐዊነትንና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ ሥራዎችም በአንደኛ፣ በመካከለኛና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 157 ሺህ ተማሪዎችን የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ተናግረዋል።

በጤና፣ በንጹሕ መጠጥ ውሃ እና በሌሎችም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የነበሩትን ፈተናዎች በመቋቋም በበጀት ዓመቱ አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን በሪፖርቱ ጠቁመዋል።
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...
Jul 28, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...
Jul 24, 2026