የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከተማው ተግባራዊ የተደረገው የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ለልማትና መልካም አስተዳደር ስኬቶች አዎንታዊ አስተዋጽኦ አበርክቷል

Aug 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ ነሀሴ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በደብረ ብርሃን ከተማ ተግባራዊ የተደረገው የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ለልማትና መልካም አስተዳደር ስኬቶች አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ።

የከተማ አስተዳደሩ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የተቋማት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ የውይይት መድረክ አካሄዷል።


በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብእሸት እንደገለጹት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሰላምን ከማስፈን ጎን ለጎን በልማትና በመልካም አስተዳደር ሥራዎች አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል።

በተለይም በሰላም ማስፈን፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ ኢንቨስትመንትን መሳብና በሌሎች የልማት ሥራዎች አበረታች ውጤት እንዲመጣ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።

አክለውም የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ሲቪል ሰርቪሱን ከብልሹ አሠራርና ከሙስና የጸዳ ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ እስክንድር ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ የተተገበሩ አዳዲስ የሪፎርም ሥራዎች የሠራተኛውን ተነሳሽነት እንዳሳደጉ ተናግረዋል።


የአገልግሎት አሰጣጥ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የተደረገው ጥረት በከተማዋ ዘርፈ ብዙ የልማት ውጤቶች እንዲመዘገቡ ማድረጉን አብራርተዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ ወይዘሮ መሠረት ምትክ በበኩላቸው፤ በሥራ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመቅረፍና አሠራርን በማሻሻል ሕብረተሰቡን በላቀ ደረጃ ለማገልገል መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

አክለውም የተገልጋዩን እርካታ ለማሳደግ መሰል የመድረክ ውይይቶች አስፈላጊ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

አሠራሮችን በማሻሻል ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የተደረገው ጥረት ለሠራተኛው ተጨማሪ ተነሳሽነትን እንደፈጠረ የገለፁት ደግሞ ሌላው አስተያየት ሰጪ አቶ አሳምነው ወልደተንሳይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026