የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በኦሮሚያ ክልል ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም በሚደረገው ጥረት ድጋፋችንን እናጠናክራለን - የሃይማኖት አባቶችና አባ ገዳዎች

Aug 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 23/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እየተደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በግንባር ቀደምትነት እንደሚደግፉ የሃይማኖት አባቶችና አባ ገዳዎች ገለጹ።

በክልሉ አደጋን በራስ አቅም የመቋቋም አቅምን ለማጠናከርና የውጭ እርዳታ ጥገኝነትን ለመቀነስ የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች በመደረግ ላይ ናቸው።

በተለይም የተፈጥሮ ድርቅ፣ ጎርፍና ሌሎች ሰው ሠራሽ አደጋዎች በሚከሰቱበት ወቅት ፈጣንና ዘላቂ ምላሽ መስጠት የሚያስችል የውስጥ አቅም የመገንባት ተግባራት ተከናውነዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የሃይማኖት አባቶችና አባ ገዳዎች፤ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

አደጋዎችን በራስ አቅም የመቋቋምና የወገንን ችግር በጋራ የመፍታት ባህል የሕዝቡ የቆየ እሴት በመሆኑ፤ ይህንኑ ባህል ከማጠናከር አንጻር ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመሆኑም ማህበረሰቡን በማስተባበር፣ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን በማጠናከርና ሀብት በማሰባሰብ ረገድ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በቁርጠኝነት እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

የሸገር ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢ አባ አፈወርቅ ዮሐንስ በበኩላቸው፤ ለሚከሰቱ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ምላሽ ለመስጠት ‘ቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ’ ያከናወናቸው ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል።

በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በማቃለል ረገድ የላቀ ሚና እንደነበረው ጠቅሰዋል።

ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉትን ስኬታማ ተግባራት በመደገፍ በኩል የሃይማኖት ተቋማት አስፈላጊውን እገዛ ማድረግ እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የ‘ቡሳ ጎኖፋ’ ስርዓት የሚበረታታ በመሆኑ የሃይማኖት ተቋማትን ጨምሮ የሁሉም አካላት ድጋፍ ሊደረግለት እንደሚገባ የገለጹት ደግሞ በሸገር ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ሼህ ሰይድ ሁሴን ናቸው።

አሰራሩ ያለምንም ልዩነት ለችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን በግንባር ቀደምትነት የሚደግፍ በመሆኑ፣ ማንኛውም በጎ ፈቃደኛ ዜጋና ተቋም አቅሙ የፈቀደውን ያህል ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

‘ቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ’ ከገዳ ስርዓት የተቀዳና የኦሮሞ ሕዝብ በደስታም ሆነ በችግር ጊዜ በጋራ የሚረዳዳበት የቆየና የዳበረ ባህላዊ እሴት መሆኑን የገለጹት ደግሞ አባ ገዳ ወርቅነህ ተሬሳ ናቸው።

ተቋሙ ለችግር የተጋለጡ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በመደገፍና አደጋዎችን በመቋቋም ረገድ ያከናወናቸው ተግባራት ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረጉ እንደሆነም ተናግረዋል።

በኦሮሚያ ክልል የዲያስፖራ አባል የሆኑት አቶ ለሜሳ ከበደ በበኩላቸው፤ ‘ቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ’ አደጋዎች ሲከሰቱ በራስ አቅም ለመቋቋምና በቂ ምላሽ ለመስጠት የሚያደርገው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል።

ይህን በራስ አቅም የመቆም ጥረት ከግብ ለማድረስም የዳያስፖራው ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በቁርጠኝነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026

የ25 ዓመት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ እና ማሻሻያ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...

Jul 28, 2026

የኢትዮጵያ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ ነው

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...

Jul 24, 2026