የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛሉ

Jul 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 11/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሰዎች ስልጠና እየወሰዱ እንደሚገኙ ተገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠናን ሐምሌ 2016 ዓ.ም ማስጀመራቸው ይታወሳል።

ስልጠናው በዋናነት በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስ እና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ ለኢዜአ እንደገለጹት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ወሳኝ ከሆኑ መሰረቶች አንዱ የዲጂታል ስነ-ምህዳሩን ማስፋት መሆኑን አንስተዋል፡፡

የዲጂታል ስነ ምህዳሩን ከሚያሰፉ ስራዎች መካከልም ዋነኛው የክህሎት ግንባታ መሆኑን ገልጸው፤ በዘርፉ እውቀትና ክህሎት ያለው የሰው ሀይል ማፍራት ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የኮደርስ ስልጠናው የዜጎችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት በማዳበር እንደሀገር የተጀመረውን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ለማሳለጥ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

በዚህም እስካሁን ባለው የስልጠናው ሂደት 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዜጎች የኮደርስ ስልጠናን እየወሰዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

እስካሁን በኢኒሼቲቩ በተሰራው ስራ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስልጠናውን ካጠናቀቁ ወጣቶች መካከል 900ሺህ የሚሆኑት የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና ሀገራዊ ተግባር መሆኑን ገልጸው፤ ክልሎችም የሚጠበቅባቸውን ድርሻ ለመወጣት እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በዚህም የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ መኖራቸውን ነው ስዩም መንገሻ ጨምረው የገለጹት።

የአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ወጣቶች በዲጂታል ኢኮኖሚ ላይ ንቁ ተሳታፊ እና አምራች እንዲሆኑ የሚያስችላቸውን ክህሎት የሚያገኙበት መሆኑንም ገልጸዋል።

በተያዘው ክረምት ወቅትም ተማሪዎች የእረፍት ጊዜያቸውን በትምህርት ቤቶችና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ስልጠናውን በመውሰድ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መልእክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026