የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የደመወዝ ማሻሻያው የሥራ ተነሳሽነታችንን ይበልጥ አጠናክሮልናል - የመንግስት ሠራተኞች 

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ ፤ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፡-መንግስት ያደረገው የደመወዝ ማሻሻያ የሥራ ተነሳሽነትን ይበልጥ በማጠናከር የተገልጋይ እርካታን ለማረጋገጥ እንዳበረታታቸው በአምቦ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች ተናገሩ።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ ተቋማት የመንግስት ሠራተኞች፤ የደመወዝ ማሻሻያው የኑሮ ውድነት ጫናን በመቀነስ በቀጣይ ሕዝቡን በላቀ ቁርጠኝነትና ብቃት ለማገልገል ብርታት እንደሆናቸው ገልጸዋል።

የከተማው አስተዳደር ትምህርት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ አቶ ጋዲሳ ደሳለኝ፤ በተደረገላቸው የደመወዝ ማሻሻያ ደስተኛ እንደሆኑ በመግለፅ ይህም የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እንደሚያግዝ ተግረዋል፡፡የሥራ ተነሳሽነታቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ያበረታታቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣትም ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የአምቦ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ አቶ ታደሰ ለገሰ በበኩላቸው፤ መንግስት ያደረገው የደመወዝ ማሻሻያ ተገቢ እና ወቅታዊ ምላሽ የሰጠ ነው ብለዋል።

ይህም ሕብረተሰቡን በበለጠ ፍጥነትና ጥራት በማስተናገድ የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ተነሳሽነታቸው እንዲጨምር እንዳበረታታቸው ገልጸዋል።

የደመወዝ ማሻሻያው የመንግስት ሠራተኞች የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም እንደሚያግዝ የገለጹት ደግሞ የአምቦ ከተማ ሴቶችና ህፃናት ጽሕፈት ቤት ሠራተኛ ወይዘሮ ትእግስት ፈይሳ ናቸው።

ማሻሻያው ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቀንስ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸው፤ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ህገ ወጦች ላይ የተጠናከረ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል።

የአምበ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አራርሳ ከበደ፤ የመንግስት ሠራተኛ የደመወዝ ማሻሻያው በከተማ አስተዳደሩ ተግባራዊ መደረጉን አረጋግጠዋል፡፡

በዚህም ሠራተኛው ደስተኛ መሆኑን አንስተው፤ ለተገልጋዩ ሕብረተሰብ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት እርካታን ለማረጋገጥ መትጋት እንዳለበት አስገንዘበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026