የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ዕውቀት ቀስመናል- የአሪ ዞን ሰልጣኞች

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ህዳር 24/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ዕውቀት መቅሰማቸውን የአሪ ዞን የኢትዮ ኮደርስ ሰልጣኞች ተናገሩ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢንሺዬቲቭ በሀገሪቱ በዲጂታል ክህሎት የታገዘ ማህበረሰብን ለመፍጠርና ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚያግዝ የኢትዮ -ኮደርስ ስልጠና በሁሉም አካባቢዎች እየተሰጠ ነው።

በስልጠናው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ የአሪ ዞን ወጣቶችም ስልጠናው የዲጂታል ክህሎታቸውን በማሳደግ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን እውቀት አንደቀሰሙ ተናግረዋል።

በዞኑ የጂንካ ከተማ ነዋሪ ገላዬ ስምዖን፥ መንግስት በነፃ ለዜጎች ያመቻቸው የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና የዲጂታል ክህሎታቸውን በማሳደግ በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውን እውቀት ማግኘታቸውን ጠቁመዋል ።

በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀትን ማሳደግ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል አቅም ለመፍጠር እንደሚያግዝ ጠቅሶ፥ ስልጠናው ዲጂታል ኢትዮጵያን በመገንባት ሀገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጥረት አጋዥ መሆኑንም ገልጸዋል።

በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና በዳታ አናሊስስ ኮርሶችን ያጠናቀቀው ገላዬ ስምኦን፥ በተለይ የዳታ አናሊስስ ኮርስ ለሁለተኛ ዲግሪ ማሟያ ለሚሰራው የመመረቂያ ፅሁፍ በእጅጉ እንዳገዛቸው አስረድተዋል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ የጂንካ ከተማ ነዋሪው ወጣት ኬብሮም ዕቁባይ በበኩሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለወጣቱ ትልቅ እድል ይዞ መምጣቱን ተናግሯል።

ስልጠናው ጠቃሚና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ዕውቀት እንደሚያስጨብጥ ገልፆ በዳታ ሳይንስ እና በፕሮግራሚንግ የሚሰጠውን ስልጠና በማጠናቀቅ ሰርተፊኬት ማግኘቱን ጠቁሟል ።

በአሪ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ የማህበራዊ ሚዲያ ሪፖርተር እየሩሳሌም ይንቲሶ በበኩሏ ስልጠናው ለጋዜጠኝነት ሙያ እጅግ አጋዥና የዲጂታል ዕውቀትን የሚያልቅ እንደሆነም ጠቁማለች።

በፕሮግራሙ ከሚሰጡ አራት ስልጠናዎች አርቲፊሻል ኢንተለጀንስና ዳታ አናሊስ ኮርሶችን ማጠናቀቋን ጠቁማ፥ በዌብ-ፕሮግራሚንግ እና የአንድሮይድ ማበልፀግ ኮርሶችን ለማጠናቀቅም ማቀዷን ገልፃለች።

ሌሎች ወጣቶችም የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማህበራዊ ሚዲያ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ እየሰራች እንዳለችም ተናግራለች።

የአሪ ዞን ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይኼነው ተስፋዬ በበኩላቸው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን ውጤታማ ለማድረግ ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገለጸዋል።

በዞኑ በሶስት ዓመታት ውስጥ ከ12 ሺህ 400 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች ስልጠናውን ለመስጠት መታቀዱን ጠቁመው ካለፈው ዓመት እስካሁን ከ4 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች ስልጠናው መሰጠቱን ጠቁመዋል።

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ቢሮ በተገኘ መረጃ መሰረት በክልሉ ከ235 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመስጠት እየተሰራ መሆኑም ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026