የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የመደመር መንግስት ለዜጎች የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ ይሰጣል

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የመደመር መንግስት ለዜጎች የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ትውልድ ተሻጋሪ የልማት ሥራዎችን እንደሚገነባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) ገለጹ።

በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ማግስት በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ አበባ ከተማን የሚመጥን አስደናቂ የልማት ስኬት መምጣቱን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሕዝባዊ መድረክ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

''የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሕዝባዊ ውይይት ተካሂዷል።


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ እና የመድረኩ ተሳታፊዎች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያን የዘመናት የብልጽግና መሻት የሚያረጋግጡ ተጨባጭ የልማት ውጤቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።

ሀገራዊ ለውጥ የወለደው የብልጽግና መንግስትም አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በሁሉም ዘርፎች ዕድገትን የሚያስቀጥል ልማት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ ባቀረቡት መነሻ ጽሁፍ፤ በሀገራዊ ለውጡ ማግስት ለመዲናዋ ነዋሪዎች የልማት ጥያቄ መልስ የሰጡ የልማት ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

የመዲናዋን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተገባው ቃል መሰረትም ከግዙፍ እስከ መካከለኛ ፕሮጀክቶችን በመገንባት የአዲስ አበባን የመልማት አቅም የገለጡ ስኬቶች መምጣታቸውን ተናግረዋል።

የገበያ ማዕከላትን በመገንባት እንዲሁም የእሁድና ቅዳሜ ገበያ ተደራሽነትን በማስፋት የመዲናዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጫና የሚያቃልልና ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገኝበት ምቹ ምኅዳር መፈጠሩንም አስረድተዋል።

በመኖሪያ ቤት፣ በኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ፣ በቱሪዝምና ኢንዱስትሪ ዘርፍ የአዲስ አበባ ከተማን ውበት በማላበስ መዲናዋን የኢትዮጵያ ብልጽግና ተምሳሌት የሚያደርጉ ለውጦች መምጣታቸውን አንስተዋል።

በቀጣይም በመደመር መንግስት የብዝኅ ዘርፍ የልማት እሳቤ የመዲናዋን ነዋሪዎች የከተሜነት አኗኗር የሚያሻሽሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሕዝባዊ ውይይት የተሳተፉ የመዲናዋ ነዋሪዎችም፤ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ለውጥ ማግስት በአጭር ጊዜ አዲስ አበባን የሚመጥን አስደናቂ የልማት ስኬት መምጣቱን ገልጸዋል።

በቀጣይም የመሠረተ ልማት ግንባታ አቅሞችንና የመልካም አስተዳደር ስኬቶችን በማስፋት የኑሮ ውድነት ጫናን የሚያቃልሉ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።


የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደገለጹት፤ መንግስት ህዝቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ዘላቂ ሰላምና ብልጽግና ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው።

ለአብነትም የመንግስትን የሰላም አማራጭ የተቀበሉ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች የኢትዮጵያ የልማት አካል እየሆኑ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

በቀጣይም የሰላም አማራጭ የሚከተሉ አካላትን ለመቀበል በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)፤ መንግስት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ትርጉም ባለው መልኩ መለወጥ የሚያስችል የልማት ስራ እየሰራ ነው ብለዋል።

ለዚህም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ተረጂነትን ለማስቀረት የ30 ቢሊየን ዶላር የጉባ ብስራት ግዙፍ የልማት ውጥኖች ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በቀጣይም የመደመር መንግሥት ዜጎች የሚያነሷቸውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ትውልድ ተሻጋሪ የልማት ስኬቶችን እንደሚያሰፋ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026