የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ጥር 29/2018 (ኢዜአ)፡-ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ ማምጣቱን የዘርፉ ምሁራን ገለፁ።

ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት በጂንካ ዩኒቨርስቲ በኮምፒውተር ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ሌንጮ ደሳለኝ እንዳሉት በዲጂታል ኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓቱን ለማዘመንና ለማሳደግ የተሰሩ ስራዎች እጅግ ውጤታማ ናቸው።


ከተቋማት ለአብነት የጂንካ ዩኒቨርስቲን የጠቀሱት ተመራማሪው በዩኒቨርስቲው ባለፉት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የመማር ማስተማር ስራውን አንድ እርከን ማሳደጉን ጠቅሰዋል።

በዩኒቨርስቲው በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የመማር ማስተማር ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰው ይህም ጥራቱን የጠበቀና በተግባር የተደገፈ ትምህርት ለመስጠት አስችሏል ብለዋል።

የፈተና አሰጣጡም በበይነ መረብ አማካኝነት መሆኑም ኩረጃና የፈተና ስርቆትን ለመከላከል እንዳስቻለ ጠቁመው የተማሪዎች የውጤት አያያዝም ከስህተት በፀዳ መልኩ በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን አስችሏል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂው በተለይ የተማሪዎችን የፈጠራ አቅም ለማሳደግ ትልቅ ሚናን እየተጫወተ እንደሚገኝም አንስተዋል።

በዩኒቨርስቲው የኤሌክትሮንክስ የትምህርት ክፍል ዳይሬክተር እና የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ መምህርና ተመራማሪ እሸቱ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ እንዳሉት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት የተጀመረው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ኢንሼቲቭ ዘመናዊ የንግድና የገንዘብ ልውውጥ እንዲስፋፋ አድርጓል።


በቴሌ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ እና በሌሎችም ፈጣን የዲጂታል የገንዘብ ልውውጦች እንዲኖሩ በማድረግ የንግድ ስርዓቱ እንዲዘምን አድርጓል ብለዋል።

በተለይ የዲጂታል መታወቂያው ወንጀልን ለመከላከል ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ለዜጎች ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችልም ጠቁመዋል።

ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር የተጣጣመ ማህበረሰብን ለመፍጠር የተጀመረው ስራና በተለይ በኢትዮ ኮደርስ የወጣቱን የዲጂታል ክህሎት ለማሳደግ የተጀመረው ርብርብ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸዋል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በሁሉም ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻሉን ጠቁመው ሀገራችን ከሌሎች ሀገራት ጋር ተወዳዳሪና ተፎካካሪ የምትሆንበትን መደላድል መፍጠሩንም አስታውቀዋል።

በተለይ በኢትዮጵያ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርስቲ ለማቋቋም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጀመረው ንቅናቄ በሀገሪቱ የቴክኖሎጂ ልህቀት እንዲመጣ ያስችላል ብለዋል።

የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በምርምር፣ በህክምና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በመከላከያ እና በሌሎች የስራ መስኮች የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026