የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢንስቲትዩቱ የዓሣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የዝርያ ማሻሻልና ተጓዳኝ ስራዎች እያከናወነ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ የካቲት 20/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሚያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የዓሣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የዝርያ ማሻሻልና ሌሎች ተጓዳኝ ስራዎች እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ተሾመ ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለጹት የዓሣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት በዓሣ ዝርያ ማሻሻያ ላይ ኢንስቲትዩቱ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

በተለይ እየተተገበረ ያለውን የዓሣ ልማት ኢንሼቲቭ ለማሳካት ምርቱን የሚጨምሩ ዝርያዎችን በስፋት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በክልሉ የውሃ አካላት በሙሉ የዓሣ ምርት መያዝ አለባቸው የሚል ግብ ተቀምጦ በዝርያ ማሻሻያ ላይ የምርምር ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።

ኢንስቲትዩቱ በምርምር ማዕከላቱ የዓሣ ጫጩት የማባዛት ስራ እየሰራ መሆኑንና የተባዙ የዓሣ ጫጩቶችን ለአርሶ አደሩ በነፃ እየተሰራጨ መሆኑንም አክለዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ከ1 ሚሊየን በላይ የዓሣ ጫጩቶች መሰራጨታቸውን ጠቅሰዋል።

በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 5 ሚሊየን የዓሣ ጫጩቶች ለማሰራጨት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የባቱ የዓሣ ምርምር ማዕከልን ጨምሮ በኢንስቲትዩቱ ስር በሚገኙ የምርምር ማዕከላት ብዛት ያላቸው የዓሣ ጫጩት ዝርያዎች መባዛታቸውን ጠቁመው የዓሣ ጫጩት ብዜት ስራው በቤተ ሙከራና በኩሬ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል።

ከዝርያ ማሻሻያ ስራዎች በተጓዳኝ ከዓሣ እርባታ ጋር በተያያዘ የእውቀትና የአሰራር ክህሎት ስልጠናና አቅም ግንባታም እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ በሀገር ደረጃ የተያዘውን በምግብ ራስን የመቻልና የስነ ምግብ ስርዓትን ለማስረፅ የዓሣ ሀብት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የጎላ ሚና አለው ብለዋል።

በዚህም የህፃናት የአእምሮ እድገት እንዲጎለብት፣ የመቀንጨርና መቀጨጭ ችግሮችን ለመቅረፍ ዓሣ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026