የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በአማራ ክልል ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ የካቲት 30/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ።

የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዓመታዊ ክልላዊ የግብርና ምርምር ስራዎች አውደ ጥናት በባህር ዳር ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል።


የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ደረጀ ማንደፍሮ በወቅቱ እንደገለጹት የ25 ዓመት የአሻጋሪ ዕድገትና ዘላቂ ልማት ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ተግባር ተገብቷል።

በመሆኑም በክልሉ የሚገኙ እምቅ አቅሞችን ለማልማት በሚደረገው ጥረት ተመራማሪዎች፣ ምሁራንና ተባባሪ አካላት በተቀናጀ መልኩ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የምርምር ስራዎች አማካይ የሰብል ምርትማነት በሄክታር ከ10 ኩንታል ወደ 32 ኩንታል ማደጉን ጠቅሰው በተለይም የስንዴ ምርታማነት ከፍተኛ ማንሰራራት እያሳየ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት የሚያሳድጉና ችግሮችን የሚፈቱ የምርምር ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

በምርምር አበረታች ውጤቶች ቢመዘገብም የአፈር አሲዳማነት፣ የግብርና መካናይዜሽን ዕጥረት፣ የድህረ ምርት ብክነትና ሌሎች ችግሮች እየተፈቱ መሄድ እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል።


የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሰማኽኝ አስረዴ(ዶ/ር)፤ ኢንስቲትዩቱ ባለፉት ዓመታት የአርሶ አደሩን ኑሮ ሊቀይሩ የሚችሉ ዘርፈ ብዙ የምርምር ስራዎች ማከናወኑን ገልጸዋል።

በዚህም በሰብልና እንስሳት ልማት፤ በአፈርና ውሃ ጥበቃ፣ በደን ልማት ስኬታማ ውጤቶች መገኘታቸውን አንስተው በምግብ ሳይንስና በባዮ ቴክኖሎጂ የተገኙ ውጤቶችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

ኢንስቲትዩቱ ግብርናውን ለማዘመን አሁን ላይ 960 የተለያዩ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አንስተው 371 የሚሆኑትን ዘንድሮ ለማጠናቀቅ መታቀዱን ተናግረዋል።


የአማራ ክልል የዩኒቨሲቲዎች ፎረም ዋና ጸሀፊ ተወካይ ጀጃው ደማሙ(ዶ/ር)፤ በበኩላቸው ከግብርና ምርምርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የአርሶ አደሩን ኑሮ የሚቀይሩና ምርታማነትን የሚያሳድጉ የምርምር ስራዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026