የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንሳዊ መረጃዎች ለማሀበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መሳለጥ ወሳኝ ደርሻ እየተወጡ ነው

Mar 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንሳዊ መረጃዎች ለማሀበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መሳለጥ ወሳኝ ደርሻ እየተወጡ እንደሚገኝ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፈጠነ ተሾመ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዓለምአቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ቀንን በኢትዮጵያ ለ45ኛ ጊዜ "ዛሬን መመልከት፤ ነገን ለመጠበቅ" በሚል መሪ ሃሳብ አክብሯል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርና በዓለም አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፅህፈት ቤት ፕሬዝዳንት ፈጠነ ተሾመ፤ የሚቲዎሮሎጂ መረጃ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መሳለጥ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል።

የሚቲዎሮሎጂ መረጃ አገልግሎት አሰጣጥን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ተቋሙ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚያከናውናቸው ስራዎች አስፈላጊ መሰረተ ልማቶች እንዲሟሉ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

የባለሙያዎችን አቅም ማጠናከር እንዲሁም ዘመኑን የሚመጥኑ ቴክኖሎጂዎች ተግባራዊ መደረጋቸውን አንስተዋል።


ኢንስቲትዩቱ የሚያቀርባቸው የአየር ትንቢያ መረጃዎች በተደራጀ፣ ትክክለኛና ተደራሽ በሆነ መንገድ በስፋት ለልማት ስራዎች አገልግሎት ላይ እየዋሉ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ከአየር ንብረ ለውጥ ጋር ተያይዞ የሚመጡ አደጋዎችን መከላከል የሚያስችሉ ስራዎች ላይ ባለድርሻ አካላት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ለ45ኛ ጊዜ የተከበረው ዓለም አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ቀን በቀጣይ በመስኩ የተሻሉ ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከርና ተደራሽነትን ለማስፋት አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

በኢንስቲትዩት የዓለም አቀፍ ጣቢያዎች ኔትወርክ ፕሮጀክት አስተባባሪ ክንፈ ኃይለማሪያም በበኩላቸው፤ የተቋማትን ትብብር በማጠናከር የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎችን በተለያዩ ቋንቋዎች ለማህበረሰቡ ተደራሽ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ኢኒስቲትዩቱ ለመረጃ ሥርጭት ቴክኖሎጂ በመጠቀም ዕድገት አስመዝግቧል ያሉት ደግሞ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ሳንታ በርበራ የምስራቅ አፍሪካ የአየር ጸባይ ሳይንቲስት ድሪባ ቆሪቻ(ዶ/ር) ናቸው።

የሚቲዎሮሎጂ መረጃዎች በሚፈለገው ልክ ጥቅም ላይ እንዲውሉ የዘርፉ ተዋናዮች የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026