🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2018 (ኢዜአ)፡- አምራች ኢንዱስትሪዎች የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ የንግድ ሚዛንን በማስጠበቅ ረገድ የጎላ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለፁ።
የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ የሚገኙ በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በቆዳ፣ በምግብ፣ በኤሌክትሮኒክስ እና በሶላር ሴል አምራች ዘርፎች የተሰማሩ ፋብሪካዎችን ጎብኝተዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ በዚሁ ወቅት፤ ከለውጡ ወዲህ ለሀገር ብልጽግና፣ ዕድገትና ተወዳዳሪነት የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ እንደ ዋና ምሰሶ ተለይቶ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።
በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመሠረተ ልማት፣ በፋይናንስ አቅርቦት ዙሪያ የነበሩ ክፍተቶች እንዲቀረፉ በመደረጉ ለአምራች ኢንዱስትሪ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት 45 ነጥብ 3 በመቶ የምርት ፍላጎት በሀገር ውስጥ ምርቶች እየተሸፈነ መሆኑን ገልጸዋል።
የወጪ ምርቶች በመጠንም በጥራትም በማደጋቸው የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ከማሳደግ ባለፈ የንግድ ሚዛንን በማስጠበቅ ረገድ የጎላ ሚና እየተጫወቱ መሆኑንም አመላክተዋል።
የዘርፉን ስኬቶች ለሕዝብ ተደራሽ በማድረግ እና ያሉ ተግዳሮቶችን በማመላከት ረገድ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እያደረጉት ያለውን ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026