የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ መጠነ-ሰፊ ስኬቶች የኢትዮጵያ መጪው ጊዜ ብሩህ ለመሆኑ አመላካቾች ናቸው

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ መጠነ-ሰፊ ስኬቶች የኢትዮጵያ መጪው ጊዜ ብሩህ ለመሆኑ አመላካቾች ናቸው ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የኢኮኖሚ ብልፅግና ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።

በብልፅግና ፓርቲ የኢኮኖሚ ብልፅግና ክላስተር የሴቶችና ወጣቶች የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።


የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የኢኮኖሚ ብልፅግና ክላስተር ሰብሳቢ አቶ መላኩ አለበል በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የመድረኩ ዋነኛ ዓላማ አባላት ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉና የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል ነው።

ምርጫው ነፃ፣ተዓማኒ፣ሰላማዊ እና ፍትሐዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሴቶችና የወጣቶች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው፤ይህም ቅቡልነት ያለው መንግሥት ለመገንባት ዓይነተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የሴቶችንና የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አመርቂ ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል።


ለአብነትም ሴቶች በፓርቲው ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ፣ ወደ አመራርነት እንዲመጡ እና በከተማም ሆነ በገጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

በሌላ መልኩ የወጣቶች የፖለቲካና የአመራርነት ድርሻ እንዲያድግ ከመደረጉም በላይ፣በስራ ዕድል ፈጠራ እና በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄና በሌሎችም ዘርፎች ያላቸው ተሳትፎ እንዲጎለብት ተደርጓል ብለዋል።

ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት ለህዝቡ የገባውን ቃል ሙሉ በሙሉ ማሳካቱ ለቀጣዩ ምርጫ ትልቅ ስንቅ እንደሚሆን ጠቁመዋል።

ባለፉት ዓመታት በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በሌሎችም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶች መጪው ጊዜ ብሩህ ለመሆኑ አመላካቾች ናቸው ብለዋል።


የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የክላስተሩ የፖለቲካ ዘርፍ ሰብሳቢ ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው፤ፓርቲው መሰረታዊ የዜጎችን ጥያቄ ከመመለስ አኳያ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል።

የዴሞክራሲ ጥያቄን ለመመለስ የሚያስችሉ ተቋማት መገንባታቸውንና እውነተኛ የዲሞክራሲ ስርዓት ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ባለፉት ዓመታት ሀገራዊ አንድነትን ከፍ የሚያደርጉ ስራዎች ተሰርተዋል፤ይህም የዳር ተመልካችነት ቀርቶ ሁሉም ዜጋ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እኩል ተሳታፊ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሁሉም እኩል ሜዳ የሚረጋገጥበት መሆኑን ጠቅሰው፣ ምርጫው ቅቡልነት ያለው የሀገረ መንግስት ግንባታን እውን ለማድረግ እንደሚረዳ አስገንዝበዋል።

ሂደቱንም ሆነ የግቡ ስኬታማነት ለማረጋገጥ በከፍተኛ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት በኢኮኖሚና በፖለቲካው ዘርፍ የተገኙ ውጤቶች መጪው ጊዜ ለብልፅግና ብሩህ እንዲሆን የሚያደርጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...

Jun 16, 2026

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026