የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የተገነባው ቪታሳሉቲ የላሜራና ቱቦላሬ ብረት ፋብሪካን መርቀዋል።

በእዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪው መስክ ባለሀብቶችን በብዛት ለመሳብ በትኩረት እየተሰራ ነው።


በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶችን ለማበረታታት በቦታ አቅርቦት፣ በመሰረተ ልማት፣ በገንዘብ ብድር እና ሙያዊ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸው፤ ይህም ለዘርፉ ውጤታማነት የራሱን አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ለአምራች ኢንዱስትሪዎች በሚደረጉ ማበረታቻዎች ምርትን በሚፈለገው ልክ የሚያቀርቡ ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪዎችን ከመገንባት ባለፈ ተኪ ምርት የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ መጥተዋል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው ዛሬ የተመረቀው ፋብሪካ በዞኑ በተኪ ምርት ላይ የተሰማራ የመጀመሪያ ግዙፍ ፋብሪካ መሆኑን ተናግረዋል።


በአካባቢው በተለያዩ የኢንቨስትመት ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ቦታዎች መዘጋጀታቸው በባለሃብቱ ተመራጭ አድርጎታል ያሉት ደግሞ የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘውዱ ዱላ ናቸው።

ፋብሪካው ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ አድርጓል ብለዋል።

የቪታሳሉቲ የላሜራና ቱቦላሬ ብረት ፋብሪካን ባለቤት አቶ ሰዒድ ሃጂ ኑሩ፤ ዘርፉን ለማሳደግ የተሰጠው ትኩረት እና የተመቻቸላቸውን ዕድል በመጠቀም ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

ለፋብሪካው ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸው፤ በሙሉ አቅሙ ወደስራ ሲገባ ለ123 ቋሚ እንዲሁም ለ273 ሰዎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...

Jun 16, 2026

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026