የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የተገነባው ቪታሳሉቲ የላሜራና ቱቦላሬ ብረት ፋብሪካን መርቀዋል።

በእዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪው መስክ ባለሀብቶችን በብዛት ለመሳብ በትኩረት እየተሰራ ነው።


በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶችን ለማበረታታት በቦታ አቅርቦት፣ በመሰረተ ልማት፣ በገንዘብ ብድር እና ሙያዊ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸው፤ ይህም ለዘርፉ ውጤታማነት የራሱን አስተዋጾ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ለአምራች ኢንዱስትሪዎች በሚደረጉ ማበረታቻዎች ምርትን በሚፈለገው ልክ የሚያቀርቡ ተወዳዳሪ ኢንዱስትሪዎችን ከመገንባት ባለፈ ተኪ ምርት የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ መጥተዋል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው ዛሬ የተመረቀው ፋብሪካ በዞኑ በተኪ ምርት ላይ የተሰማራ የመጀመሪያ ግዙፍ ፋብሪካ መሆኑን ተናግረዋል።


በአካባቢው በተለያዩ የኢንቨስትመት ዘርፍ ለሚሰማሩ ኢንቨስተሮች መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ቦታዎች መዘጋጀታቸው በባለሃብቱ ተመራጭ አድርጎታል ያሉት ደግሞ የእዣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘውዱ ዱላ ናቸው።

ፋብሪካው ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ አድርጓል ብለዋል።

የቪታሳሉቲ የላሜራና ቱቦላሬ ብረት ፋብሪካን ባለቤት አቶ ሰዒድ ሃጂ ኑሩ፤ ዘርፉን ለማሳደግ የተሰጠው ትኩረት እና የተመቻቸላቸውን ዕድል በመጠቀም ወደ ስራ መግባታቸውን ተናግረዋል።

ለፋብሪካው ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸው፤ በሙሉ አቅሙ ወደስራ ሲገባ ለ123 ቋሚ እንዲሁም ለ273 ሰዎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጠር አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026