🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስር ጽኑ መሰረት መጣሉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ዛሬ መጋቢት 24 ቀን በጉለሌ ክፍለ ከተማ 6ተኛውን አዲስ መሶብ ዲጂታል አንድ ማዕከል በይፋ መርቀዋል።

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት መጋቢት 24 ቀን ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሻገር ቃል ኪዳን የተገባበት ታሪካዊ ቀን ነው።
ሀገራዊ ለውጡ የመጣው ለሁሉም፣ ከሁሉምና በሁሉም ዜጋ ተሳትፎ መሆኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ ከለውጡ ወዲህ የሚታዩና ተጨባጭ የሆኑ በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡት በጋራ ጥረታችን ነው ብለዋል።
ይህ ለውጥ የፖለቲካ፣ የማህበራዊና የኢኮኖሚ ስብራቶቻችን እንዲጠገኑና ወደ ከፍታ እንድንጓዝ እጅግ ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት “እንሰራለን፤ እንችላለን!” በሚል መርህ በጋራ በተነሳንባቸው ጊዜያት፣ ከኋላ ቀር የፖለቲካ ባህሎች ተላቀን ችግሮችን በውይይትና በምክክር የመፍታት ሂደት ላይ መገባቱን ከንቲባዋ አመልክተዋል።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሽግግር ወደ ዘመናዊ እና ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚ ለመገንባት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውንም ነው ያነሱት።
በማህበራዊ ዘርፍም የተሰበሩ እሴቶችን በማከም ማህበራዊ ፍትህ እንዲነግስ የሚስችሉ በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን ተናግረዋል።
በተለይም በከተማዋ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወገኖችን፣ የሀገር ባለውለታዎችን፣ አቅመ ደካሞችን፣ አካል ጉዳተኞችንና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ከአስቸጋሪ ኑሮ አውጥተን የሰውን ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲኖሩ አድርገናል ብለዋል።
በትምህርት ዘርፍም ባዶ ምሳ ዕቃ ይዘው ወደ ትምህርት ገበታ ይመጡ የነበሩ ሕፃናትን እኩል በልተውና ለብሰው እንዲማሩ ከማድረግ ባለፈ፣ አዲስ አበባን ሕፃናትን ለማሳደግ ተመራጭ ከተማ ለማድረግ መቻሉን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።
ሌላው ትልቅ ስኬት የመንግስት የተቋማት ስብራትን በመጠገን ነፃ፣ ገለልተኛና የአገልጋይነት መንፈስን የተላበሱ ጠንካራ ተቋማትን የመገንባት ሽግግር መሆኑን ገልጸዋል።
ለዘመናት የአገልግሎት ዘርፉን ለመለወጥ ሳይቻል ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትቦ የኖረ ቢሆንም፣ የለውጡ መንግስት ቃል በገባው መሰረት ችግሩን ሥር ነቀል በሆነ መልኩ የሚለውጥ 'መሶብ' ዲጂታል አንድ ማዕከልን በመተግበር ለተገልጋዩ እፎይታን ይዞ መምጣቱን አመልክተዋል።
የእነዚህ የለውጥ ፍሬዎች ዋንኛ ተጠቃሚ የሆነው የአዲስ አበባ ነዋሪም ማልዶ ወደ አደባባዮች በመውጣት የዘወትር ድጋፉን እንደገና ማጽናቱን ከንቲባዋ ተናግረዋል።
ጅማሬያችን ትላንት ቢሆንም ከህዝባችን ጋር ያሳካነው ድል እና የደረስንበት ርቀት ቀላል አይደለም ሲሉም አክለዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ ሊያስቆም የሚችል ምንም ዓይነት ምድራዊ ኃይል እንደሌለ በመልዕክታቸው ላይ አስፍረዋል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026