የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የአዘርባጃን የአሳን ቀላል የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎትን ጎበኙ

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከዓለም የከተሞች ፎረም ተሳትፎ ጎን ለጎን የአዘርባጃን የአሳን ቀላል የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎትን ጎብኝተዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኢትዮጵያ ልዑክ ከዓለም የከተሞች ፎረም ተሳትፎ ጎን ለጎን የአዘርባጃንን የ“አሳን” (ASAN-Azerbaijan Service and Assessment Network) ቀላል የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት መጎብኘቱን ጠቁመዋል።

ከንቲባዋ ባስተላለፉት መልዕክት፥ በኢትዮጵያ እስከአሁን በመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከፍተኛ ለውጥ የመጣ ቢሆንም፣ አሁንም ልምድ ሊሆኑ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል።


ከ14 ዓመታት በፊት የተጀመረውና በቀን 40 ሺህ አፕሊኬሽን ላይ አገልግሎት የሚያሳልጠው “አሳን”፣ በአውቶቡሶች የሚሰጥ የገጠር አካባቢዎች ተንቀሳቃሽ የአገልግሎት ማዕከል በተደራጀ፣ ፈጣንና ቀላል መንገድ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

በኢትዮጵያም ከ41 በላይ ማዕከላት ተገንብተው ስራ የጀመሩ ሲሆን፣ ከነዚህም ውስጥ በአዲስ አበባ 6 ማዕከላት እና 1 ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙም ነው ከንቲባዋ ያወሱት።

በጉብኝቱ ወቅትም የ“አሳን” ሰራተኞች አገልግሎት ሲሰጡ ፈገግታ እና ትህትና አንዱ የአገልግሎት መለኪያ መሆኑን፣ የመከታተያ ካሜራዎች የተገጠሙ መሆኑን እና በጥሩ ሁኔታ የሚያገለግል ሰራተኛ ተመዝኖ የተገልጋዩ የዕርካታ መጠን ከፍተኛ ከሆነ ከደሞዝ በተጨማሪ ቦነስ እንደሚከፈለው ለመታዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።


በዛው ልክ ደግሞ በመስፈርቱ መሰረት ያላገለገለ ሰራተኛ ወዲያው እንደሚባረርና ለነገ ተስፋ አድገው ህዝባቸውን በከፍተኛ ትጋትና አክብሮት የሚያገለግሉ በርካታ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችንም መመልከታቸውን ገልጸዋል።

የእኛም ቢሮክራሲ በተጀመረው አግባብ ሙሉ በሙሉ እንደሚለወጥ እናምናለን ያሉ ሲሆን ይህ እንዲሳካም በትጋት እንደሚሰራ ከንቲባዋ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026