🔇Unmute
ድሬደዋ፣ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፡- በድሬደዋ ባለፉት አስር ወራት ከ17ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን የአስተዳደሩ ስራና ክህሎት ቢሮ ገለፀ።
ቢሮው በበጀት ዓመቱ በአነስተኛና ጥቃቅን ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ከ112 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፍጠሩንም ጠቁሟል።
በቢሮው የስራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በበጀት ዓመቱ የስራ ዕድል ለመፍጠርና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተከናወኑ የተቀናጁ ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል።
በአስተዳደሩ በተደረገው እንቅስቃሴም በበጀት ዓመቱ አስር ወራት ከ17ሺህ 300 በላይ ለሚሆኑ ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት ለተመረቁ ወጣቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል።
ለተገኘው ውጤት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ እየመጣ የሚገኘው እመርታ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በመጠቆም።
በተጨማሪም ግብርና፣ ኮንስትራክሽን እና የአገልግሎት ዘርፎች የስራ ዕድል የተፈጠረባቸው መስኮች መሆናቸውን አቶ ሰኢድ ገልጸዋል።
በአስተዳደሩ የሚገኙ የተማሩ ወጣቶችን ጥያቄዎች ከአጋር አካላት ጋር በመቀናጀት የመመለስ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አክለዋል።

እንደ አቶ ሰኢድ ገለፃ ቢሮው በዘንድሮ በጀት ዓመት በስሩ በተደራጁት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመታገዝ በአነስተኛና ጥቃቅን የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ድጋፎች አድርጓል።
የብድር፣ አጫጭር የሙያና የክህሎት ስልጠና እንዲሁም ከሚመለከታቸው ሴክተሮች ጋር በመቀናጀት የመስሪያና የመሸጫ ቦታዎች ማመቻቸቱን ለአብነት ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም ከ600 በላይ ለሚሆኑ ኢንተርፕራይዞች ከ112 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ በማድረግ የዕድገት ሽግግርን እንዲያፋጥኑ መሰራቱን አንስተዋል።
በስራ ዕድል ፈጠራውም ሆነ በገበያ ትስስር ሴቶች እና አካል ጉዳተኞች ትኩረት ማግኘታቸውንም ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026