የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በቅመማ ቅመም ምርት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራር እየተስፋፋ ነው

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቴፒ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ በቅመማ ቅመም ምርት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የምርት ዝግጅት ሂደትን የማስፋፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል አስታወቀ።

ማዕከሉ የእርድ ምርትን ለገበያ ለማቅረብ የሚደረገውን ልማዳዊ አሰራር የሚያስቀር አዲስ ቴክኖሎጂ ለአርሶ አደሮች አስተዋውቋል።


የእርድ ምርትን በባህላዊ መንገድ ለማዘጋጀት የሚደረገው የመቀቀል ሂደት ከፍተኛ የእንጨት፣ የውሃ፣ የጊዜና የጉልበት ብክነትን የሚያስከትል እንደሆነ ተገልጿል።

የቴፒ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ደረጀ ቱሉ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ባደረገው የምርምር ሥራ ያስተዋወቀው አዲስ ቴክኖሎጂ የምርቱን ጥራት በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያስጠብቅ ነው።


በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ ምርት ለማቅረብ ጥራት ትልቅ ትርጉም እንዳለው የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ አዲሱ የእርድ ማዘጋጃ ማሽን ጊዜና ጉልበትን በእጅጉ የሚቆጥብ መሆኑን አስረድተዋል።

የቅመማ ቅመም ምርቶችን በብሔራዊ ደረጃ የሚያስተባብረው ይህ ማዕከል፤ የእርድ ሰብልን በክልሉ በስፋት ማስተዋወቁን ገልጾ፣ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ የማሰራጨት ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

በማዕከሉ የቅመማ ቅመም ምርት ብሔራዊ አስተባባሪና ተመራማሪ የሆኑት አቡኪያ ጌቱ በበኩላቸው፤ አዲሱ የእርድ መክተፊያ ማሽን ከዚህ ቀደም ሦስት ሳምንታት ይፈጅ የነበረውን የምርት ዝግጅት ጊዜ ወደ 5 ቀናት ዝቅ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።


በላብራቶሪ በተደረገ ፍተሻ በማሽኑ የተዘጋጀው ምርት የተሻለ የጥራት ደረጃ መያዙ መረጋገጡንና ይህም ለሀገር ውስጥና ለዓለም ገበያ ከባዕድ ነገሮች የጸዳ ምርት ለማቅረብ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።

የሸካ ዞን ግብርና፣ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ አዳምሰገድ ኃይለኢየሱስ ፤ በዞኑ ካለው ከ4 ሺህ ሄክታር በላይ የእርድ ማሳ፣ በዓመት ከ20 ሺህ ቶን በላይ ምርት ለማዕከላዊ ገበያ እንደሚቀርብ ተናግረዋል።

ማዕከሉ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ከማቅረብ ባለፈ፣ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂዎችን ማስተዋወቁ ትልቅ ፋይዳ ያለው በመሆኑ፤ አርሶ አደሮች ተደራጅተው ማሽኑን መጠቀም የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡ አርሶ አደሮችም፤ ነባሩ የእርድ ዝግጅት ሂደት የማገዶ፣ የውሃ እና የጉልበት ብክነት ስለሚያስከትል እስካሁን ከምርቱ ተገቢውን ጥቅም እንዳላገኙ ገልጸዋል።


በተጨማሪም የተቀቀለው እርድ ደርቆ ለገበያ እስኪበቃ ረጅም ጊዜ ይወስድ እንደነበር አስታውሰው፤ ማዕከሉ ያስተዋወቀውን ማሽን በመጠቀም ምርታቸውን በቀላሉ አዘጋጅተው ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ለገበያ ለማቅረብ ትልቅ ተስፋ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

የእርድ ምርት ለምግብ ዝግጅት፣ ለአልባሳት ማቅለሚያና ለፊት መዋቢያዎች ግብዓት ሆኖ የሚያገለግል ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጥቅም ያለው የቅመማ ቅመም ዓይነት መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026