የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ ለማቅረብ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቃሉ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ ለማቅረብ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለፁ።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን ዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክት ዛሬ መርቀዋል።


በፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በክልሉ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በተለይም ግብርናውን በሜካናይዜሽን፣ በቴክኖሎጂና በአዳዲስ አሰራር በማዘመን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ የሚቀርብ ምርት ለማምረት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ የገፀ ምድርና የከርሰ ምድር ውሃ በስፋት እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ ይሄን የውሃ ሀብት ለመስኖ ልማት በማዋል ዓመቱን ሙሉ የማምረት ሥራው ይጠናከራል ብለዋል።

ለእዚህም በክልሉ በርካታ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በቃሉ ወረዳ ዛሬ የተመረቀው ፕሮጀክትም ለእዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቱ በደቡብ ወሎ ዞን የቃሉ ወረዳ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የደዋጨፋ ወረዳን በጋራ የልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ፋይዳው የጎላ ነው ሲሉም አክለዋል።

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ በበኩላቸው እንዳሉት፣ የመስኖ መሰረት ልማቶችን በማስፋፋት አርሶ አደሩ ከዝናብ ጠባቂነት ተላቆ በመስኖ ጭምር በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ በማምረቱ ውጤት እያስገኘ ነው።


በቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር ተገንብቶ ዛሬ የተመረቀው የመስኖ ፕሮጀክት ከ290 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችልና ከ490 በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል።

ግንባታው በሰባት ወራት ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁ የመንግስትን ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ ጀምሮ የመፈጸም ብቃት ያሳያል ብለዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፤ በዞኑ የሚገነቡ በርካታ የመስኖ ፕሮጀክቶች ምርታማነትን በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ዛሬ የተመረቀው የመስኖ ፕሮጀክት አርሶ አደሩ በዓመት ሦስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ የሚያስችለው መሆኑን የገለጹት ደግሞ የቃሉ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን አህመድ ናቸው።

በምረቃው ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026