የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ ለማቅረብ የተጀመረው ሥራ ይጠናከራል

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቃሉ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ ለማቅረብ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) ገለፁ።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር የተገነባውን ዲርማ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክት ዛሬ መርቀዋል።


በፕሮጀክቱ ምረቃ ላይ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በክልሉ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በተለይም ግብርናውን በሜካናይዜሽን፣ በቴክኖሎጂና በአዳዲስ አሰራር በማዘመን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ የሚቀርብ ምርት ለማምረት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ የገፀ ምድርና የከርሰ ምድር ውሃ በስፋት እንደሚገኝ ጠቅሰው፣ ይሄን የውሃ ሀብት ለመስኖ ልማት በማዋል ዓመቱን ሙሉ የማምረት ሥራው ይጠናከራል ብለዋል።

ለእዚህም በክልሉ በርካታ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በቃሉ ወረዳ ዛሬ የተመረቀው ፕሮጀክትም ለእዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቱ በደቡብ ወሎ ዞን የቃሉ ወረዳ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የደዋጨፋ ወረዳን በጋራ የልማት ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ፋይዳው የጎላ ነው ሲሉም አክለዋል።

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ደረጀ ማንደፍሮ በበኩላቸው እንዳሉት፣ የመስኖ መሰረት ልማቶችን በማስፋፋት አርሶ አደሩ ከዝናብ ጠባቂነት ተላቆ በመስኖ ጭምር በዓመት እስከ ሦስት ጊዜ በማምረቱ ውጤት እያስገኘ ነው።


በቃሉ ወረዳ በ365 ሚሊዮን ብር ተገንብቶ ዛሬ የተመረቀው የመስኖ ፕሮጀክት ከ290 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ ለማልማት የሚያስችልና ከ490 በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል።

ግንባታው በሰባት ወራት ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁ የመንግስትን ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ ጀምሮ የመፈጸም ብቃት ያሳያል ብለዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፤ በዞኑ የሚገነቡ በርካታ የመስኖ ፕሮጀክቶች ምርታማነትን በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ዛሬ የተመረቀው የመስኖ ፕሮጀክት አርሶ አደሩ በዓመት ሦስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ የሚያስችለው መሆኑን የገለጹት ደግሞ የቃሉ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን አህመድ ናቸው።

በምረቃው ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮችና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026