የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በደቡብ ኦሞ ዞን በዘንድሮው የበልግ እርሻ ለገበያ ተኮር ሰብሎች ትኩረት ተሰጥቷል

Jun 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ግንቦት 21/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኦሞ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ለገበያ ተኮር ሰብሎች ትኩረት በመስጠት መሰራቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የደቡብ ኦሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንላርገው አዲሱ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በዞኑ በዘንድሮ የበልግ እርሻ 108 ሺህ ሄክታር መሬት መልማቱን ገልጸዋል።


አጠቃላይ ከለማው መሬት ወደ 4 ሚሊዮን የሚጠጋ ምርት ለማግኘት እንደታቀደም ጠቅሰዋል።

በዘንድሮ የበልግ እርሻ ለገበያ ተኮር እና የኢንዱስትሪ ግብዓት ለሚሆኑ ስንዴ፣ ሰሊጥ፣ ካሳቫ እና ማሾ ሰብሎች ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።

ቀደም ሲል አርሶና አርብቶ አደሩ ውስን ሰብሎችን ብቻ በማልማት ለገበያ የሚያቀርብበትን ሁኔታ በመቀየር ገበያ ተኮር የሆነ አመራረት በመከተል በኩታ ገጠም በስፋት የሚያለሙበት ሁኔታ ተፈጥሯል ብለዋል።

ከዚህም ባሻገር አርሶና አርብቶ አደሩ በአካባቢው ያልተለመዱ እንደ ሩዝ እና ካሳቫ ምርቶችን ማምረት መጀመራቸውን አንስተው፥ በዚህም የገቢ አቅማቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።


በዞኑ ሳላማጎ ወረዳ ገሮ ቀበሌ በካሳቫ ምርት የተሰማሩት አርሶ አደር አለሙ ላስታ፥ በዘንድሮ የበልግ አዝመራ 17 ሄክታር መሬት ላይ ካሳቫ እያለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል ።

መንግስት የእርሻ መሬት እና የእርሻ ትራክተር በማቅረብ እገዛ እያደረገላቸው መሆኑን ገልፀው፥ የግብርና ባለሙያዎችም ገበያ ተኮር የሆኑ ሰብሎችን እንዲያለሙ ሙያዊ ድጋፍ እያደረጉላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ካሳቫ በአንድ ሄክታር እስከ 300 ኩንታል ምርት የሚያስገኝ እና ቶሎ የሚደርስ ሰብል መሆኑ ደግሞ ይበልጥ ተመራጭ አድርጎታል ነው ያሉት አርሶ አደሩ።


ሌላው የወረዳው አርሶ አደር አድማሱ ጩሉ፥ በዘንድሮ የበልግ አዝመራ በኩታ ገጠም 8 ሄክታር መሬት ላይ ሩዝ እያለሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ሩዝ ውሃ በሚተኛባቸው ረግረጋማ ቦታዎች ምርት የሚሰጥ በመሆኑ ሩዝ እያለሙ መሆኑን ገልጸዋል።

በአካባቢው ቀደም ሲል በቆሎ እና ማሽላ በስፋት የማልማት ልምድ እንደነበር ጠቁመው፥ አሁን ላይ በመንግሥት ድጋፍ ገበያ ተኮር የሆኑ ሰብሎችን በማልማት የተሻለ ገቢ ማግኘት መጀመራቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026