የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን ትብብር ይበልጥ ያጠናክራል

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደህንነት ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክረው በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) ገለጹ።

ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቅድሚያ የሚሰጠው የሉዓላዊነት ጉዳይ ነው።

ጥያቄው በሁሉም መመዘኛ ተገቢ ነው ያሉት አማካሪው፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄን ለማንሳት ጠንካራ የታሪክ እና የሕግ መሰረት እንዳላት አመልክተዋል።

ይህ የባህር በር የማግኘት እንቅስቃሴ ብሔራዊ ጥቅምን የማረጋገጥ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ ሆኗል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በተለያዩ መድረኮች የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በሰፊው የማስገንዘብ ሥራ ማከናወኗን ገልጸዋል።

በዚህም ጥያቄው በዓለም አቀፍ መድረክም ከጊዜ ወደ ጊዜ እውቅና እያገኘ መምጣቱን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በቀጣናው የኢኮኖሚ ዕድገትን፣ ትስስርን እና መረጋጋትን በመምራት ረገድ ታሪካዊ ሚና ያላት ሀገር መሆኑን የገለጹት ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ ለቀጣናው ሠላምና መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።

የቀጣናው ሀገራት ትስስርን በማጠናከር ረገድም የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሠላም ለጎረቤት ሀገራት ሰላም እውን መሆን ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው፤ የአፍሪካ ቀንድን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ሁኔታ መሠረታዊ በሆነ መልኩ በማረጋጋት ቀጣናዊ ብልፅግና እውን እንዲሆን አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...

Jun 16, 2026

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026