የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን ትብብር ይበልጥ ያጠናክራል

Jun 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 7/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደህንነት ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክረው በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) ገለጹ።

ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቅድሚያ የሚሰጠው የሉዓላዊነት ጉዳይ ነው።

ጥያቄው በሁሉም መመዘኛ ተገቢ ነው ያሉት አማካሪው፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄን ለማንሳት ጠንካራ የታሪክ እና የሕግ መሰረት እንዳላት አመልክተዋል።

ይህ የባህር በር የማግኘት እንቅስቃሴ ብሔራዊ ጥቅምን የማረጋገጥ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ ሆኗል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በተለያዩ መድረኮች የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊና በሰጥቶ መቀበል መርህ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በሰፊው የማስገንዘብ ሥራ ማከናወኗን ገልጸዋል።

በዚህም ጥያቄው በዓለም አቀፍ መድረክም ከጊዜ ወደ ጊዜ እውቅና እያገኘ መምጣቱን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በቀጣናው የኢኮኖሚ ዕድገትን፣ ትስስርን እና መረጋጋትን በመምራት ረገድ ታሪካዊ ሚና ያላት ሀገር መሆኑን የገለጹት ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ ለቀጣናው ሠላምና መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።

የቀጣናው ሀገራት ትስስርን በማጠናከር ረገድም የኢትዮጵያ ወደ ባህር በር መመለስ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሠላም ለጎረቤት ሀገራት ሰላም እውን መሆን ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው፤ የአፍሪካ ቀንድን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ሁኔታ መሠረታዊ በሆነ መልኩ በማረጋጋት ቀጣናዊ ብልፅግና እውን እንዲሆን አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026