የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ከተቋቋመ ጀምሮ ከአባል የፋይናንስ ተቋማት 20 ነጥብ 61 ቢሊየን ብር አረቦን ሰብስቧል

Jun 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ከተቋቋመ ጀምሮ ከአባል የፋይናንስ ተቋማት 20 ነጥብ 61 ቢሊየን ብር አረቦን መሰብሰቡን የፈንዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ደሳለኝ አምባው (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡

የፈንዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ደሳለኝ አምባው (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የመድን ፈንዱ በተቋቋመ አጭር ዓመታት ውስጥ ለአባል የፋይናንስ ተቋማት አማራጭና ውጤታማ የፋይናንስ ሥርዓት ፈጥሯል።

ከአባል ፋይናንስ ተቋማት አርቦን መሰብሰብ፣ የተሰበሰበን አርቦን በመንግስት ግምጃ ቤት ሰነድ ኢንቨስትመንትን ማሳደግና አንድ የፋይናንስ ተቋም ቢወድቅ ተቋሙን በመተካት ለገንዘብ አስቀማጮች ከ90 ቀናት ባነሰ ጊዜ መክፈል የሚያስችሉ ዋና ዋና ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ውጭ ሁሉም የግል ባንኮችና ሁሉም የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ አባል መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን ባለው ከአባል የፋይናንስ ተቋማት 20 ነጥብ 61 ቢሊየን ብር አረቦን መሰብሰቡን አስታውቀዋል።

ከዚህ ውስጥ 18 ነጥብ 72 ቢሊዮን ብር ከመደበኛ ተቀማጭ ገንዘብ የተሰበሰበ ሲሆን፤ ቀሪው 1 ነጥብ 89 ቢሊዮን ብር ደግሞ ከወለድ ነጻ ተቀማጭ ገንዘብ የተሰበሰበ መሆኑን አስረድተዋል።

የፈንዱ አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ክምችትም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ89 ነጥብ 76 በመቶ ብልጫ በማሳየት 22 ነጥብ 98 ቢሊየን ብር መድረሱን አንስተዋል።

ከጠቅላላ ኢንቨስትመንቱ 20 ነጥብ 97 ቢሊየን ብር በመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ ላይ ውሏል፤ ቀሪው 2 ነጥብ 01 ቢሊየን ብር ደግሞ በሙዳራባህ የቁጠባ ኢንቨስትመንት ሂሳብ መቀመጡን አስታውቀዋል።

በ2018 በጀት ዓመት 9 ነጥብ 35 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ በታቀደው መሠረት፤ እስካለፈው ዘጠኝ ወር 6 ነጥብ 76 ቢሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ የተሰበሰበውን አርቦንም በአግባቡ ኢንቨስትመንት ላይ በማዋል የፋይናንስ ተቋማትን ጤናማነትና ተወዳዳሪነት የሚያጎለብት አቅም እየተገነባ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ተጠሪነቱን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በማድረግ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 482/2013 መቋቋሙ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ከብሔራዊ ባንክ፣ ከኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበርና ከኢትዮጵያ የማይክሮ ፋይናንስ ማኅበር በተውጣጡ አምስት የዳይሬክተሮች ቦርድ የሚመራ ተቋም ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026