የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የቱሪዝም ዘርፉን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማዘመን እየተሰራ ነው

Jun 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዲጂታል ቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም የቱሪዝም ዘርፉን ለማዘመን እየሰራች መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትር ዴኤታው ከዓለም አቀፉ የብራንዲንግ እና ሚዲያ ተቋም "FAME by Sheeraz" መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ሺራዝ ሀሰን እና የልዑካን ቡድናቸው ጋር በቱሪዝም ዘርፍ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

እንደገና አበበ (ዶ/ር) መንግስት ባለፉት ስምንት ዓመታት አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመገንባት፣ ነባሮቹን በማደስ እና የዲጂታል ቴክኖሎጂን (Visit Ethiopia Portal) በመጠቀም ዘርፉን ለማዘመን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም አዲስ አበባን የአህጉሪቱ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጥረት ጠቅሰው፤ እንደ "FAME by Sheeraz" ባሉ ተቋማት አማካኝነት የኢትዮጵያን የቱሪዝም ሀብቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ማስተዋወቅ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የ"FAME by Sheeraz" መስራች ሺራዝ ሀሰን በበኩላቸው፣ ድርጅታቸው በአሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በመካከለኛው ምስራቅ ታዋቂ ግለሰቦችን እና የንግድ ምልክቶችን በማስተሳሰር የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳለው ገልጸዋል።

ይህንን ልምድ በመጠቀም የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት በጋራ ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹት ዋና ስራ አስኪያጁ፤ ለተግባራዊነቱም ተቋሙ በአዲስ አበባ ቋሚ ጽሕፈት ቤት እንደሚከፍት ጠቁመዋል።

በተጨማሪም በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታገዙ የመገናኛ ብዙኃን አማራጮችን በመጠቀም ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ስትራቴጂያዊ እቅድ ቀርጸው ለመንቀሳቀስ ዝግጁ መሆናቸውን ነው ዋና ስራ አስኪያጁ ያረጋገጡት።

በውይይቱ ወቅት፣ በሁለቱ ወገኖች መካከል የተነሱትን ነጥቦች ወደ ተግባር ለመቀየር ስምምነት ላይ መደረሱን የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት አምጥተዋል -ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...

Jun 16, 2026

የሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት ከምስል ጋር!

  የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...

Jun 4, 2026

በዲጂታል ክህሎት ራሳችንን እያበቃን ነው - ተማሪዎች

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...

Jun 1, 2026

በኦሮሚያ ክልል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ የአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት ተሰጥቷል

አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...

May 25, 2026