🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦የሰው ሰራሽ አስተውሎትና ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አስተማማኝ የሃይል አቅርቦት እንዲፈጠር እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ገለጹ፡፡
ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ለኢዜአ እንዳሉት፤ አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት መስመሮችንና የዲስትሪቡዩሽን ትራንስፎርመሮችን ብቃት ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው።
የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግርን ለመፍታት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትን የማሻሻል፣ መልሶ የማቋቋምና የቅድመ-መከላከል ጥገና ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ድንገተኛ ብልሽቶችን አስቀድሞ ለመለየትና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመዘርጋትም ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ጥቅም ላይ እየዋሉ መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪከ አገልግሎት፣ ከመንግሥትና የልማት አጋሮች የሚመነጭ የገንዘብ ሃብትን በመጠቀም መሰረተ ልማት የማሻሻል ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ከመሠረተ ልማት ግንባታው ጎን ለጎንም የደንበኞችን አገልግሎት ጥራትና ፍጥነት ማሻሻል የሚያስችሉ ሰፋፊ የትራንስፎርሜሽን ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል።
አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን በመተግበር የኔትወርክ አቅምን የማሳደግ፣ መልሶ የማደራጀትና የቅድመ-መከላከል ጥገና ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።
ደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻልም የውስጥ አቅምን የማጠናከርና የጥገና ቡድኖችን በአዲስ መልክ የማደራጀት ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የተፈጠረው ውጤታማ የደንበኞች አገልግሎትም ውጤታማነትን እያሻሻለ መሆኑን አስረድተዋል።
አገና፤ ሰኔ 8/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች የሚደረጉ ማበረታቻዎች አመርቂ ውጤት ማምጣታቸውን የ...
Jun 16, 2026
የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢን...
Jun 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 20/2018(ኢዜአ)፦ በአምስት ሚሊየን የኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር በመታገዝ በዲጂታል ክህሎት ራሳቸውን እያበቁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን...
Jun 1, 2026
አዳማ፤ግንቦት 16/2018(ኢዜአ)፦በክልሉ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ለአሰራር ማሻሻያና ለተቋማት ግንባታ ትኩረት መሰጠቱን በብልፅግና ፓርቲ የኦ...
May 25, 2026