የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የዩኒቨርሲቲው የኢንኩቤሽን ማዕከል የፈጠራና ክህሎት ውጤቶችን የምናስተዋውቅበት ምቹ ምኅዳር ፈጥሮልናል 

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የኢንዱስትሪ ኢንኩቤሽን ማዕከል የቴክኖሎጂ ፈጠራና ክህሎት ውጤቶችን ለኢንዱስትሪዎች የሚያስተዋውቁበት ምቹ ምኅዳር እንደፈጠረላቸው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ሙያተኞች ገለጹ።

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የፈጠራ ሙያተኞችን ከኢንዱስትሪዎችና አጋሮች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ የፈጠራ ሥራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ማስተዋወቂያ መድረክ ማካሄዱ ይታወቃል።


በመድረኩም በዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪያል ኢንኩቤሽን ማዕከል በተማሪዎችና በተመራማሪዎች የተሰሩ የፈጠራና ክህሎት ውጤቶች ቀርበዋል።

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ከማል ኢብራሂም (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኢንኩቤሽን ማዕከሉ ለተማሪዎችና የፈጠራ ሙያተኞች ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።


የማዕከሉ ዋና ዓላማ ተማሪዎች የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ፈጣሪና ኢንተርፕርነር የሚሆኑበትን ዓለም አቀፍ መደላድል መፍጠር መሆኑን አብራርተዋል።

በዚህም የዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪ ኢንኩቤሽን ማዕከል ተማሪዎችን፣ ተመራማሪዎችንና ኢንዱስትሪዎች በአንድ ቦታ የሚገናኙበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር እንዳስቻለ አስረድተዋል።

የስሪ ዲ ፕሪንቲንግ ዲጂታል ኮንስትራክሽን የቤት መሥሪያ ማሽን ያለሙት ዮሐንስ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ ማዕከሉ የፈጠራ ባለቤቶችንና የኢንዱስትሪ አጋሮች በቀጥታ የሚገናኙበትን ወሳኝ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።


ለዕይታ ያቀረቡት የስሪ ዲ ዲጂታል ኮንስትራክሽን ማሽንም በኮምፒውተር የታገዘ ዲዛይንን ወደ ማሽን ቋንቋ በመቀየር በውስን የሰው ሃይል ጊዜ ቆጣቢና ጥራት ያለው ግንባታን ማከናወን እንደሚያስችል ገልጸዋል።

የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ የፈጠራ አቅምን መጎልበት የአሰራር ሥርዓቶችን በራስ አቅም በማሳለጥ ዘመናዊ ተግባራትን ለማከናወን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።

ሌላኛው የፈጠራ ባለቤት ወጣት ሳሙኤል አለሙ በበኩሉ፤ በሀገር በቀል የምህንድስና ዕውቀት የለስላሳ መጠጦችን መሸጥና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ተንቀሳቃሽ የቬንዲንግ ማሽን ማልማቱን ገልጿል።

የቬንዲንግ ማሽኑም የሁሉንም ባንኮች የክፍያ አማራጭና የደንበኞችን ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ በማንኛውም ሰዓት ያለአንዳች ኃይል መቆራረጥ ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ተናግሯል።

ቬንዲንግ ማሽኑ ለትምህርትና ጤና ተቋማት ጭምር ተመራጭና ዘመናዊ አገልግሎት የሚሰጥ ነው ብሏል።

ተማሪዎችም በትምህርት ቤት ቆይታቸው የሚያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በማጎልበት ለሚስተዋሉ የቴክኖሎጂ ክፍተቶች መፍትሔ መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026