የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የቦንጋ ከተማን እድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው 

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- የቦንጋ ከተማን ዕድገትና ልማት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የካፋ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።

የከተማ አስተዳደሩ ለቀጣይ አሥር ዓመታት ተግባራዊ የሚያደርገው የቦንጋ ከተማ ስትራክቸራል ማስተር ፕላን ላይ ያተኮረ የሕዝብ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።


ይህ አዲስ ስትራክቸራል ፕላን የከተማዋን የመሠረተ ልማት አቅርቦት፣ የመኖሪያ ቤት ፍላጎት፣ የአረንጓዴ ስፍራዎችን አጠባበቅ እና የኢንዱስትሪ ቀጠናዎችን በዘመናዊ መንገድ ለመምራት የተነደፈ መሆኑም ተገልጿል።

ዕቅዱ በቀጣይ አሥር ዓመታት ከተማዋን በፕላን በመምራት በዘፈቀደ የሚደረጉ ግንባታዎችን ለመግታትና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ለመዘርጋት ትልቅ መሠረት ይጥላል ተብሎም ይጠበቃል።

በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ፤ የቦንጋ ከተማ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠረች እድሜ ጠገብ ከተማ መሆኗን ተናግረዋል።

ከተማዋ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ ሳታድግ መቆየቷን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ አሁን ላይ መንግሥት ለከተሞች ዕድገት ከሰጠው ልዩ ትኩረት በመነሳት፣ የቦንጋን ዕድገት በማፋጠን ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የከተማዋን ፕላን በአዲስ መልክ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ ከኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ጋር ውል በመግባት ሰፊ ጥናትና ምርምር ሲደረግ መቆየቱን ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

ፕላኑ ላይ ከዚህ ቀደም የተለያዩ የውይይት መድረኮች ሲደረጉ መቆየታቸውን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፤ በዛሬው የሕዝብ መድረክ ላይ የሚሳተፉ የኅብረተሰብ ክፍሎችም አስፈላጊውን ሐሳብና አስተያየት በመስጠት ለከተማዋ ዕድገትና ልማት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

ቦንጋ ከተማ ደረጃዋን የጠበቀችና ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ(ዶ/ር) የገለጹ ሲሆን፤ አዲሱ ማስተር ፕላንም ለዚህ ስኬት ትልቅ ድርሻ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።


አዲሱ ስትራክቸራል ፕላን የአካባቢውን ሥነ-ምህዳር መሠረት ያደረገ መሆኑን የጠቀሱት ከንቲባው፤ ከተማዋን ለልማት፣ ለመኖሪያ ቤት፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ ከማድረግ ባለፈ የገቢ አቅሟን የሚያሳድግ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ከዚህም ባሻገር ፕላኑ ለሕብረተሰቡን የረጅም ጊዜ የመልማት ፍላጎት ምላሽ የሚሰጥ መሆኑን ከንቲባው ገልጸው፤ አሁን እየተካሄደ ያለው ውይይት አስፈላጊ ግብዓቶችን በማካተት ፕላኑ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

ለሚቀጥሉት አሥር ዓመታት የሚያገለግለው ይህ አዲስ ፕላን፤ የከተማዋን ነባር 6 ሺህ 300 ሄክታር ስፋት ወደ 15 ሺህ ሄክታር በላይ ያሳደገ መሆኑ በውይይቱ ላይ ተመልክቷል።

በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026