የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በሐረሪ ክልል በቱሪዝም ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ቅርሶችን በመታደግ የሐረርን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻነት እያጎለበቱ ነው

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):- በሐረሪ ክልል በቱሪዝም ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት ቅርሶችን በመታደግ የሐረርን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻነት ማጎልበቱን የክልሉ ቱሪዝም ኮሚሽን ገለጸ።

መንግሥት ያዘጋጀው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ-ግብር ከለያቸው አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ምሰሶዎች መካከል ቱሪዝም አንዱ ነው።

ከዚህ ቀደም ዘርፉ በበቂ ሁኔታ ሳይለማና የገቢ ምንጭነቱ ሳይጎለብት በመቆየቱ፣ አሁን ላይ ሀገራዊ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማሳደግ እና የሥራ ዕድል ለመፍጠር እንደ ዋና ሞተር ተለይቶ እየተሰራበት ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ቱሪዝም አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር!” በሚል በሰጡት ማብራሪያም በዘርፉ ልማት የተከናወኑ ተግባራትንና የመጡ ውጤቶችን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው፤ የብዝሃ የኢኮኖሚ አማራጮችን መሰረት አድርጎ በመስራት በተለይም በቱሪዝም ዘርፍ የተመዘገበውን ስኬት በማሳያ አስቀምጠዋል።


የጥንት ውበታቸውን ከዘመናዊ ገጽታ ጋር በማሰናሰል የቱሪዝም መዳረሻ እንዲሆኑ በለውጡ መንግሥት እንደ አዲስ ከተገነቡና ከተሻሻሉ የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ የሐረር ከተማ ቀዳሚዋ ነች።

የሐረር ጀጎል ግንብና በውስጡ የሚገኙት ጥንታዊ፣ ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ቅርሶች ከኢትዮጵያ አልፎ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ሀብት መሆናቸው ይታወቃል።

በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ እየተተገበረ ያለው የኮሪደር ልማትና የቅርሶች እድሳት ስራ፣ የታሪካዊቷን ሐረር ከተማ የቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ በማነቃቃት ለአካባቢያዊና ሀገራዊ ኢኮኖሚው አዲስ አቅም እየፈጠረ ይገኛል።

የክልሉ የቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሚ አብዱልዋሲ እንደገለጹት፣ በክልሉ ያለውን የቱሪዝም ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርና እምቅ አቅሙን ለመጠቀም መጠነ-ሰፊ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።


የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት የተከናወኑት ተግባራትም ለአደጋ ተጋርጠው የነበሩ ቅርሶች እንዲለሙና ይዘታቸውን ጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ ማስቻላቸውን ኮሚሽነሩ ገልጸው፤ ይህም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አቅም ፈጥሯል።

በዘርፉ በተሰጠው ትኩረት የቱሪዝም መስህቦችን በማልማት፣ የጎብኚዎችን ቆይታ በማራዘምና ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ አቅም በማሳደግ ረገድ የተሻሉ ተግባራት የተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በዘንድሮ ዓመት ክልሉን የጎበኙ የውጭ ቱሪስቶች ቁጥር ካለፈው ዓመት የ47 በመቶ ብልጫ ማሳየቱን የገለጹት ኮሚሽነሩ፤ ይህም መሠረተ-ልማቶች ሲሟሉ የቱሪዝም ዘርፉ የኢኮኖሚው ዋነኛ ምሰሶ እንደሚሆን አመላካች ነው ሲሉ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ሳሚ ገለጻ፣ የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት የተከናወኑት ተግባራት ከውጭ ሀገር ቱሪስቶች ባሻገር የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች፣ የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ሌሎች አካላት ሐረርን እንዲጎበኙና ውበቷን ለዓለም እንዲያስተዋውቁ ሰፊ ዕድል ፈጥሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026