የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የንግድ ባዛሩ ለአምራቾች ምርትን ከማስተዋወቅ ባለፈ የገበያ ትስስር እየፈጠረ ነው

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ):-በወልቂጤ ከተማ የተከፈተው የንግድ ባዛርና አውደ ርዕይ ምርቶቻቸውን ከማስተዋወቅና ከመሸጥ ባለፈ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እያገዛቸው መሆኑን አምራቾችና ኢንተርፕራይዞች ገለጹ።

ለሦስት ቀናት በሚካሄደው አውደ ርዕይ እና ባዛር ላይ ከ120 በላይ አምራቾች የግብርና፣ የኢንዱስትሪ እና የእደ ጥበብ ምርቶችን ይዘው ቀርበዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ አምራቾችና ኢንተርፕራይዞች እንዳሉት አውደ ርዕዩና ባዛሩ ምርቶቻቸውን ለማስተዋወቅና ለመሸጥ እንዲሁም ለቀጣይ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ከባዛሩ እና አውደርዕዩ ተሳታፊዎች መካከል የዳሪም ዱቄት ፋብሪካ የሰው ሃብትና ንብረት አስተዳደር ማናጀር አቶ ወንድምአገኝ ታሪኩ፣ ጥራት ያላቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ይዘው መቅረባቸውን ገልጸዋል።

ቀደም ባሉት ጊዜያት በተለያዩ አካባቢዎች በተዘጋጁ ባዛርና አውደ ርዕይ ላይ ሲሳተፉ መቆየታቸውን ገልጸው፣ ይህም የገበያ ዕድልን ለማስፋትና ደንበኛ ለማፍራት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

ከወልቂጤ ማረሚያ ተቋም የተለያዩ የእደ ጥበብ ውጤቶች ይዘው በባዛሩ ላይ የተሳተፉት አቶ አብድልከሪም ጀማል በበኩላቸው፤ በባዛሩ የተፈጠረላቸው የገበያ ዕድል ምርቶቻቸውን በመሸጥ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ማረሚያ ተቋሙ ታራሚዎችን በስነ ምግባር ከማነጽ ባለፈ የተለያየ ሙያ ባለቤት እንዳደረጋቸው ገልጸው፣ በኢንተርፕራይዝ በማደራጀት ለብዙዎች የሥራ ዕድል ፈጥሮ ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን ተናግረዋል።


የንግድ ባዘሩና አውደ ርዕዩ አምራቹን ከሸማቹ ማህበረሰብ ጋር በማገናኘት ተጠቃሚ እያደረጋቸው መሆኑን የገለጹት ደግሞ የፍኸር ጨርቃጨርቅ ማኑፋክቸሪንግ ማህበር ሰብሳቢ ወይዘሮ ዚኪራ ሙራድ ናቸው።

ኢንተርፕራይዞች እርስ በርስ ልምድ ከመለዋወጥ ባለፈ የገበያ ዕድል ለማግኘት ማስቻሉን ገልጸው፣ በባዛሩ ከሌሎች ጋር የገበያ ትስስር እየፈጠሩ መሆኑንም ተናግረዋል።

በባዛሩ ላይ ግብይት ሲፈጽሙ የነበሩት የከተማዋ ነዋሪ ወይዘሪት አሰለፈች አህመድ በበኩላቸው፤ የእደ ጥበብ ውጤቶችን ጨምሮ የተለያዩ ቁሶችን በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ ጊዜያት የሚዘጋጁ ባዛርና አውደርዕዮች ሸማቹን ከአምራቹ ጋር ስለሚያገናኙ ሁለቱንም ተጠቃሚ ያደርጋል ያሉት ነዋሪዋ፣ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።


በወልቂጤ ከተማ ለሦስት ቀናት በተዘጋጀው የንግድ ባዛርና አውደ ርዕይ ከ120 በላይ አምራቾች የግብርና፣ የኢንዱስትሪ እና የእደ ጥበብ ውጤቶችን ይዘው ቀርበዋል ያሉት ደግሞ የጉራጌ ዞን ሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙራድ ያሲን ናቸው።

እሳቸው እንዳሉት ባዛር እና አውደርዕዩ የገበያ ትስስር ለመፍጠር፣ ልምድ ለመለዋወጥ እና የእርስ በእርስ ግንኙነትን ለማጠናከር ያለመ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026