የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በዞኑ ከ20 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል 

Jul 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቤንች ሸኮ ዞን በበጀት ዓመቱ ከ20 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩን የዞኑ ሥራና ክህሎት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ኮጁ በዳካች ለኢዜአ እንዳሉት፤ የአካባቢውን ጸጋ መሠረት በማድረግ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲቻል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው።

በዚህም በ2018 በጀት ዓመት ከ20 ሺህ የሚበልጡ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት።

የስራ እድል የተፈጠረላቸው ዜጎች በግብርና ፣ በማኑፋክቸሪንግ እና አገልግሎት ዘርፍ እንዲሰማሩ በማድረግ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል።


የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራን ለማጠናከርም የመስሪያና መሸጫ ቦታ፣ የመነሻ ብድር ፣ የገበያ ትስስር ፣ የህይወት ክህሎት ስልጠናን ጨምሮ በተቀናጀ መልኩ የተከናወኑት የክትትልና ድጋፍ ስራዎች ውጤት አስገኝተዋል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ ወደስራ ለገቡ ወጣቶች ከ163 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር መሰራጨቱንም ነው የጠቀሱት።

የአካባቢውን ጸጋ በማልማት ወደ ሀብት ቀይሮ መጠቀም እንዲቻል በግብርና ላይ ትኩረት መደረጉን ጠቅሰው፤ ወጣቶቹ በተለይ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ላይ በስፋት መሰማራታቸው ስኬት እንዲመዘገብ አድርጓል ብለዋል።

ከሥራ ዕድል ተጠቃሚዎች መካከል በሚዛን አማን ከተማ የ"ዕድገት ዶሮ እርባታ" ማኅበር ሰብሳቢ ወጣት ገበየሁ ሽፈራው ከተማ አስተዳደሩ ባመቻቸላቸው የመስሪያ ቦታ በመጠቀም 1 ሺህ የሥጋና የእንቁላል ዶሮዎችን እያረቡ መሆኑን ተናግሯል።


በተሰማሩበት መስክ ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ የዘርፉን ገበያ ለማረጋጋት እየተቻለ መሆኑን ነው ያስታወቀው።

በቀጣይም ስራውን በማስፋት የበግና የወተት ላሞች እርባታ ላይ ለመሰማራት ማቀዳቸውን ነው ያመለከተው።

የ"ዕድገት ለሰላም" ማኅበር ሰብሳቢ ሚሚ በላቸው በበኩላቸው፤በተያዘው ዓመት በማህበር በመደራጀት በእንቁላል ምርት ላይ በመሰማራት ውጤታማ መሆናቸውን አስረድተዋል።


ከተማ አስተዳደሩ እያደረገ ባለው የመስሪያ ቦታ ድጋፍን ጨምሮ የክትትልና ድጋፍ ስራዎች ለውጤታማነታቸው ጉልህ ድርሻ እንዳለው ነው ያመለከቱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026