የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በምስራቅ ጎጃም ዞን በመኸር እርሻ ከ485 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም ይለማል

Jul 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦በምስራቅ ጎጃም ዞን በመጭው የመኸር ምርት ዘመን ከ485 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም እርሻ እንደሚለማ የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ እንቢአለ አለኽኝ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ከ669 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ ከ485 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በኩታ ገጠም እንደሚለማ ነው የተናገሩት።

በመኸር እርሻ የምርት ማሳደጊያ ግብአት ፣ ቴክኖሎጂና አዳዲስ አሰራሮችን በተሻለ መንገድ ተግባራዊ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ ነው።

በዚህም አርሶ አደሩ ከራሱ አልፎ ለገበያ የሚያቀርበው ትርፍ ምርት ለማምረት እንደሚችልም ነው የተናገሩት።


ከ100 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማሳተፍ የስንዴ፣ ጤፍ ፣ ማሽላ ፣ የቢራ ገብስ ፣ በቆሎና ቦለቄ ሰብሎችን በኩታ ገጠም ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን በተደረገው ጥረትም ክረምቱ ቀድሞ በገባባቸው አካባቢዎች ከ90 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን ተናግረዋል።

በኩታ ገጠም ልማቱ ከ20 በላይ ትራክተሮች በእርሻ ስራው ላይ መሰማራታቸውን ጠቁመው ይሕም የአርሶ አደሩን ጊዜ፣ ገንዘብና ጉልበት በመቆጠብ በሌሎች የልማት ስራዎች እንዲሰማራ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

እስካሁን በኩታ ገጠም በዘር ለተሸፈነው መሬትም ከ250 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን ይህም ምርታማነትን በማሳደግ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት የሚያግዝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በዞኑ የደብረኤሊያስ ወረዳ የገነቴ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አየነው በቀለ እንደገለጹት፤አንድ ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም በማልማት በቆሎ መዝራታቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው ዓመትም በኩታ ገጠም ካለሙት ስንዴና በቆሎ ያገኙትን ተጨማሪ ምርት ለገበያ በማቅረብ የኢኮኖሚ አቅማቸውን ማሳደጋቸውን አስረድተዋል።

የደጀን ወረዳ የኩራር ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ያደለው በዛ በበኩላቸው፤ ባለፈው የምርት ዘመን ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በኩታ ገጠም ማሽላ በመዝራት ተጨማሪ የአራት ኩንታል ምርት እንዳገኙ ነው የሚገልጹት።

በዘንድሮ ዓመትም ተጠቃሚነታቸውን ለማስፋት በአካባቢው ካሉ አርሶ አደሮች ጋር በጋራ በመሆን በኩታ ገጠም ማሽላን መዝራታቸውን አብራርተዋል።

የኩታ ገጠም አሰራር ዘርንና ግብአት አጠቃቀምን በተመሳሳይ ጊዜ ከማካሄድ ባሻገር የሚዛመት የሰብል በሽታን፣ አረምንና ተባይን በጋራ ለመከላከል የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

በዞኑ በመኸር ምርት በአጠቃላይ ከሚለማው ከ669 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ከ26 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መታቀዱንም ነው ያመለከቱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026