የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በታሪኩ ከፍተኛ የሆነውን የ50 ነጥብ 27 ቢሊየን ብር ግብይት ፈጸመ

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለፈው የበጀት ዓመት የ50 ነጥብ 27 ቢሊየን ብር ግብይት በመፈጸም በታሪኩ ከፍተኛውን ስኬት ማስመዝገቡን ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መርጊያ ባይሳ አስታወቁ።

ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መርጊያ ባይሳ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ 214 ሺህ ቶን የግብርና እና የግብርና ያልሆኑ ምርቶች ለገበያ ቀርበው ተገበያይተዋል።

በዚህም ተቋሙ በታሪኩ ያስመዘገበው ከፍተኛው የኢኮኖሚ አፈጻጸም ሆኖ ተመዝግቧል።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለፈው የበጀት ዓመት የ50 ነጥብ 27 ቢሊየን ብር ግብይት በመፈጸም በታሪኩ ከፍተኛውን ስኬት ማስመዝገቡን ነው ዋና ስራ አስፈጻሚው የገለጹት፡፡

ቀደም ሲል ተቋሙ በ2011 በጀት ዓመት ያከናወነው የ40 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ግብይት በከፍተኛ ስኬትነት ይጠቀስ የነበረ ቢሆንም፣ የዘንድሮው የልማት ዕቅድና አፈጻጸም ግን ያንን በላቀ ደረጃ በመብለጥ ስኬታማ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከግብይቱ በተጨማሪ የምርት ገበያው ያስቀመጣቸውን ግቦች በከፍተኛ ሁኔታ መፈጸም የተቻለበት በጀት ዓመት እንደነበረ ገልጸዋል።

ከነዚህም መካከል የመጋዘን ደረሰኝ ብድር በማመቻቸት 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ለአርሶ አደሮች፣ ለህብረት ስራ ዩኒየኖችና ለአቀነባባሪዎች ማስተላለፍ መቻሉን ገልጸዋል።

ይህም አርሶ አደሩ ምርቱን አስይዞ ሌላ ተጨማሪ ማስያዣ ሳይፈልግ የአጭር ጊዜ የገንዘብ ፍላጎቱን እንዲያሟላ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም የምርት ገበያው ባቋቋመው አካዳሚ አማካኝነት 795 ሰልጣኞችን በቡና ቅምሻ፣ በጥራጥሬና ቅባት እህሎች ጥራት ምርመራ እንዲሁም በአዲስ የኤክስፖርት ማመቻቸት መስክ 46 ሰልጣኞችን ማሰልጠን መቻሉን አብራርተዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም ቀደም ሲል ሻጮችና ገዢዎች በአካል በመገኘት ብቻ ያከናወኑት የነበረውን ግብይት ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን ማዛወር ተችሏል ሲሉ ገልፀዋል።

ይህም ባለድርሻ አካላት ከቤታቸው ወይም ከቢሯቸው ሆነው ያለምንም እንግልት ግብይት እንዲፈጽሙ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የምርት ገበያው የግብርና እና የግብርና ያልሆኑ ምርቶችን ጨምሮ ወደ 28 የሚጠጉ የምርት አይነቶችን ለማገበያየት የሚያስችለውን የውል ማዕቀፍ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ጠቁመዋል።

በስንዴ ኢኒሼቲቭ አርሶ አደሮችና ማህበራት ምርታቸውን በመጋዘን ደረሰኝ ብድር በማስያዝ ያለ ገንዘብ እጥረት ማገበያየት መጀመራቸውን ገልጸዋል።

ይህ አሰራር አምራቾችን በፋይናንስ በመደገፍ የገበያ ትስስሩን ያሳለጠ ታላቅ የልማት ስኬት መሆኑን ዋና ስራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026