የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ የሚያስችል የአሰራርና የቴክኖሎጂ አቅም ገንብታለች 

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ የሚያስችል የህግ፣ የአሰራርና የቴክኖሎጂ አቅም መገንባቷን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ገለፀ።

ከትናንት ሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የቆየው ዓለም አቀፉ የፓርላማ የመረጃ ደኅንነት ፎረም ተጠናቋል።


በመድረኩ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም፣ የሳይበር ደኅንነት፣ ቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ፣ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርና መሰል ዓለም አቀፍ አሳሳቢ ጉዳዮች ላይ በስፋት ምክክር ተደርጎበታል።

በዚህ ወቅት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዳንኤል ጉታ እንዳሉት፤ የሳይበር ደህንነት ስጋቶች ድንበር የለሽ በመሆናቸው ስጋቶችን ለመከላከል ዓለም አቀፍ ህጎችን የማጣጣምና የቅንጅት ስራ ወሳኝ ነው።

ሃገራት የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅና የሚቃጡ ጥቃቶችን ለመከላከል ተናባቢ ህጎች ሊኖራቸው እንደሚገባ አንስተው፣ ኢትዮጵያም በዚህ አግባብ እየሰራች መሆኗን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚያስችል የህግ፣ አሰራርና ቴክኖሎጂ አቅምን ገንብታለች ብለዋል።

ፎረሙ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ መድረኮችን ለማዘጋጀት ያላትን አቅም ለማሳየትና ለገጽታ ግንባታ አስተዋፅኦ የሚያበረክት መሆኑንም ተናግረዋል።


የናይጄሪያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፎረሙ አባል አግበዲ ዬቲዬኔ ፍሬድሪክ (ዶ/ር) ፤ በኢትዮጵያ በተዘጋጀው ፎረም መሳተፋቸው ከተለያዩ ሀገራት ልምድ ለመለዋወጥ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።


በህንድ በሚገኘው የካሊንጋ የኢንዱስትሪ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ቫሩን ሱትራ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ ፎረሙን ሙያዊ በሆነ አግባብ መምራቷ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026