የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአፍሪካን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የሚያሳልጥ የዲጂታል አቅም መገንባት ያስፈልጋል 

Jul 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦የአፍሪካን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት የሚያሳልጥ የዲጂታል ሥርዓት መገንባት እንደሚያስፈልግ የአፍሪካ ህብረት ገለጸ።

የአፍሪካ የትምህርት ፈጠራ ኤክስፖ 2026 በአፍሪካ ህብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

''የትምህርት ዲጂታል ሽግግርና የፈጠራ መፍትሔዎችን ማሳደግ'' በሚል መሪ ሃሳብ ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ኤክስፖ የፈጠራ ባለቤቶች፣ የጥናትና ምርምር ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያን ክምቢና በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በአፍሪካ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ብቁ የሰው ሃይል መገንባት ያስፈልጋል።

ለዚህም በአፍሪካ ሕብረት በተገባው የፖለቲካ ቁርጠኝነት መሰረት አፍሪካዊያን በተለወጠ ዓለም ውስጥ የትውልዱን ዕውቀትና ክህሎት ለማዳበር በትኩረት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የአፍሪካን ትምህርት ወደ ዲጂታል ማሸጋገር ወቅታዊ እና የሀገራትን ትኩረት የሚፈልግ ነው ብለዋል።

በአፍሪካ አካታች የዲጂታል ትምህርት ስርአት በመዘርጋት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ፣ የዲጂታል የትምህርት ግብዓቶችን ማሟላት ላይም ይበልጥ መስራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

ትምህርትን በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተቃኘ ማድረግ እና የአስተማሪዎችን የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግ ትምህርትን ለማሸጋገር ቁልፍ ጉዳይ መሆኑንም አክለዋል።

የጥናትና ምርምር ተቋማትን አቅም ማሳደግም የሀገራት የትኩረት ማዕከል ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የአፍሪካ ህብረትም በአህጉሪቱ ትምህርትን ለማዘመን የሚሰሩ ተግባራትን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026