🔇Unmute
ሀረር ፤ሐምሌ 9/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል በበጀት ዓመቱ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች መሰረት በማድረግ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ አስታወቁ።
ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የክልሉ ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት እንዳመለከቱት፥ በክልሉ በበጀት ዓመቱ የተቀመጡ የልማት እቅዶችን ለማሳካት ጥረት ተደርጓል።

በየደረጃው ያለው አመራር፤ ፈፃሚና መላው ህብረተሰብ እቅዱን ለማሳካት ከፍተኛ ተሳትፎና ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አንስተዋል።
በዚህም በኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች ፈጣንና ዘላቂ ልማት ለማምጣት፤ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ለማዘመን እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት አበረታች ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
በከተማና በገጠና የኮሪደር መሠረተ ልማቶችን የማስፋፋት ተግባራት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ሆነው በመከናወናቸው ውጤት መገኘቱን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ጥራት፣ተሳትፎና ተደራሽነትን የማጎልበት እንዲሁም የተማሪዎች ውጤት የማሻሻል ስራም ውጤታማ መሆኑን አንስተዋል ።
በክልሉ ዘላቂ ሰላምና ጸጥታ ለማስፈንና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም የፍትሕ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በተከናወኑ ተግባራት አመርቂ ውጤት መገኘቱን አመልክተዋል።

ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ተረጂነትን ለማስቀረት፣ የስራ እድል ፈጠራን ለማጎልበት፣ ክልሉ የሚያመነጨውን ገቢ ከመሰብሰብ፣ በጤናና በሌሎች የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል ።
እንዲሁም በክልሉ የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራዎችም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ እድገት ማሳየታቸውን ተናግረዋል።
ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው የምክር ቤቱ ጉባኤ የተለያዩ ሪፖርቶች፣ እቅዶችና ሹመቶች ይጸድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...
Aug 28, 2026
መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...
Aug 18, 2026
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...
Aug 10, 2026
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 20, 2026