የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ብልሹ አሰራርን እያስቀረ ነው

Jul 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ፤ ሐምሌ 11/2018(ኢዜአ)፦ የነቀምቴ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የተገልጋዩን እንግልትና ብልሹ አሰራርን እየቀረፈ መሆኑን ኢዜአ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ።

ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ሻምበል ኦላና ጉደታ፤ መንግስት የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ማስጀመሩ እጅግ ጠቃሚ ሆኖ እንዳገኙት ተናግረዋል።


ይህ አሰራር የምንፈልገውን አገልግሎት በአጭር ጊዜ እንድናገኝ እያገዘን ነው ያሉት ነዋሪው፣ በተለይም ቀደም ሲል በአንዳንድ መስሪያ ቤቶች የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር አሁን መቀረፉን ገልጸዋል።


ሌላኛው ነዋሪ አቶ ተመስገን ነጋሽ፤ በመንግስት መስሪያ ቤቶች የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች የረጅም ጊዜ የመልካም አስተዳደር ጥያቄያችን ነበር ብለዋል።

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከዚህ ቀደም ይታዩ የነበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ቀርፏል ነው ያሉት።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ተገልጋዩ ጊዜውን፣ ጉልበቱንና ገንዘቡን እንዳያባክን እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን የገለጹት ደግሞ አቶ ደገፉ ቶለሳ ናቸው።

ከዚህ ቀደም ረጅም ጊዜ ይውስዱ የነበሩ መንግስታዊ አገልግሎቶች በአጭር ጊዜ መፍትሄ ሲያገኙ መመልከታቸውንም ተናግረዋል።


የነቀምቴ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኃላፊ በየነ ቀናቴ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀልጣፋ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን፣ አጠቃላይ ሂደቱም በቴክኖሎጂ የተደገፈ ነው ብለዋል።

ይህንን ስራ ውጤታማ ለማድረግ በማዕከሉ 25 የተለያዩ ተቋማት ተካተው አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን 117 ሰራተኞችም መመደባቸውን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በማዕከሉ 98 የተለያዩ የአገልግሎት አይነቶች እየተሰጡ መሆኑን ጠቅሰው፣ ማዕከሉ ስራ ከጀመረ ወዲህ ተገልጋዩ ጉዳዩን በአጭር ጊዜ እየፈጸመ ወደ መደበኛ ስራው እየተመለሰ ይገኛል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026