የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን በማስፋፋት ለሀገር እድገትና ማንሰራራት መሰረት እንዲሆን ይሰራል- ርእሰ መስተዳድር እንደሻው ጣሰው (ዶ/ር)

Jul 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳእና፤ ሐምሌ11/2018 (ኢዜአ )፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን በማስፋፋት ለሀገር እድገትና ማንሰራራት መሰረት እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በሆሳዕና ከተማ በግማሽ ቢሊየን ብር ወጪየተገነባውን የዓለም የከረጢት ፋብሪካን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት በክልሉ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉን በማስፋፋት ለሀገር እድገትና ማንሰራራት መሰረት እንዲሆን ጥረት እየተደረገ ነው።

በዚህም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን የማቋቋምና ዘርፉን የማበረታታት ስራ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ተናግረዋል ።

በዘርፉ ተኪ ምርትን በማምረት የውጪ ምንዛሬ ከማስገኘት ባለፈ የስራ እድል እንዲፈጠር እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል ።

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢን በመፍጠር የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በዘርፉ የሚሰማሩ ባለሀብቶችን በመደገፍ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።

ዘርፉን በመደገፍ የከተሞችን እድገትና የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።


የሀድያ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ሀላፊ አቶ ደነቀ ጊቻሞ በበኩላቸው የመደመር መንግስት ለግል ዘርፉ በሰጠው ትኩረት በርካታ አምራች ኢንደስትሪዎች ወደ ስራ እየገቡ ነው ብለዋል።

በዚህም የዘርፉ ተኪ ምርቶችን የማምረት፣ የውጪ ምንዛሬን የማስገኘትና የስራ እድል የመፍጠር አቅም መጎልበቱን ተናግረዋል።

የፋብሪካው ባለቤት አቶ ፀደቀ ጌታቸው በበኩላቸው ፋብሪካው በግማሽ ቢሊየን ብር ወጪ መገንባቱን ተናግረዋል ።


ፋብሪካው ከ350 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠር መቻሉንም አንስተዋል ።

በፋብሪካው በተፈጠረለት የስራ እድል በሚያገኘው ገቢ ራሱንና ቤተሰቡን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የገለጸው ደግሞ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተመረቀው ወጣት ዮናስ መለሰ ነዉ።

በምረቃ ስነ ስርአቱ ላይ የክልል፣ የሀድያ ዞንና የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026