🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ባለፉት አምስት ዓመታት በልማትና በመልካም አስተዳደር የተመዘገቡ ስኬቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት ዋና ተጠሪ ኢብራሒም ዩሱፍ ገለጹ።
የአስተዳደሩ ምክርቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ኢብራሒም ዩሱፍ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል።
በተለይ የገጠርና የከተማ ነዋሪዎችን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተቀናጀ መንገድ ለመፍታት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል።
የድሬዳዋን የንግድ፣ የኢንዱስትሪ እና የአገልግሎት ማዕከልነት በተጨባጭ ያረጋገጡ አዳዲስ አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ ሆቴሎችና የሎጅስቲክ ማሳለጫ ማዕከላት ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን አስረድተዋል።
በተለይ በመጀመሪያው ምዕራፍ በከተማዋ ዋና ዋና አካባቢዎች ከ16 ኪሎ ሜትር በላይ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ድሬዳዋን ጽዱ፣ ውብና ለኑሮ ተመራጭ እያደረጋት መምጣቱን ገልጸዋል።
ታሪካዊ ቅርሶችን በጠበቀና ገጽታዋን በሚገነባ መልኩ የተከናወነው የኮሪደር ልማት በከተማዋ አዳዲስ መሠረተ ልማቶች እንዲስፋፉ ማድረጉንም ጠቁመዋል።
መሰረተ ልማቶቹ ባለሀብቶችን ከመሳብ በተጨማሪ የትራፊክ መጨናነቅን በማስቀረት የተሽከርካሪ አደጋን ለመቀነስ አስችለዋል ብለዋል።
በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የፌደራልና የአስተዳደሩ ተቋማት ተቀናጅተው ፈጣንና ቀልጣፋ ዲጂታል አገልግሎት በመስጠታቸው የዘመናት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን እየፈታ መሆኑንም አቶ ኢብራሒም ተናግረዋል።
እንደ እሳቸው ገለጻ በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የኢንዱስትሪና የግብርና ምርቶችን ለሕብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የኑሮ ውድነትን ማቅለል የሚያስችል ውጤታማ ሥራ ተከናውኗል።
በአስተዳደሩ አገልግሎት መስጠትና ማምረት በጀመሩ ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች በብዙ ሺህ ለሚገመቱ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መቻሉንም የመንግስት ዋና ተጠሪው አንስተዋል።
በኢንተርፕራይዝ የተደራጁ ወጣቶችን ውጤታማ ለማድረግ የስልጠና፣ የመስሪያ ቦታ፣ የብድርና የሙያ ድጋፍ መሰጠቱንም አመልክተዋል።
ባለፉት 5 ዓመታት በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን በላቀ ደረጃ ለማሳደግ አስተዳደሩ የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩንም አቶ ኢብራሒም ተናግረዋል።
አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...
Jul 21, 2026
አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...
Jul 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና የዲጂታል አገልግሎት መስፋፋት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ትብብርን ለማጠና...
Jul 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦የብሔራዊ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የሀብት ልየታ ጥናት ውጤታማ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንትን ለማጠናከር እንደሚያስችል የኢ...
Jul 8, 2026