የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የኢትዮጵያ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ የማቋቋም ርዕይ ሀገሪቱን የአፍሪካ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል ያደርጋታል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ (AIU) የማቋቋም ርዕይ ሀገሪቱን የአፍሪካ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ማዕከል የሚያደርግ ታሪካዊ እርምጃ መሆኑን የአፍሪካ ኅብረት የትምህርት ክፍል ኃላፊ ሶፊያ አሺፓላ ገለጹ።

ኢትዮጵያ የጀመረችውን ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ ዲጂታል ቴክኖሎጂን የኢኮኖሚ ምሰሶና የልማት ማሳለጫ መሣሪያ በማድረግ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበች ትገኛለች።

የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂና የአምስት ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ መርሐ ግብርም የዜጎችን የዲጂታል፣ የሰው ሠራሽ አስተውሎትና የዳታ ሳይንስ ዕውቀትና ክህሎት የሚያበለጽግ አቅም እየፈጠሩ ነው።

የዲጂታላይዜሽን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የመንግሥት አገልግሎቶችን ጥራትና ተደራሽነት በማረጋገጥ በቁልፍ የኢኮኖሚ መሣሪያነት በማገልገል ስኬት አስገኝቷል።

የአፍሪካ ኅብረት የትምህርት ክፍል ኃላፊ ሶፊያ አሽፓላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በዲጂታል ቴክኖሎጂ መስክ ወሳኝ መደላድል በመፍጠር አበረታች ውጤት እያመጣች ነው።

በተለይም የሰው ሠራሽ አስተውሎትን ልማት ለማፋጠን ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የወሰደችው ተነሳሽነት ከፍተኛ አድናቆት የሚቸረው መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የተጀመረው የዲጂታል ቴክኖሎጂ ልማት አብዮትም በሌሎች የአፍሪካ አገራት ተመሳሳይ ኢንቨስትመንቶች እንዲስፋፉ በር የሚከፍት ታሪካዊ ክስተት እንደሆነ አንስተዋል።

ይህም በአፍሪካ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ልማት የለውጥ ጉዞ ላይ ትልቅ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ የማቋቋም ርዕይ የወደፊቱን ትምህርትና ምርምር በተሻለ ጥራት በመቅረጽ አገሪቱን ፈር ቀዳጅ እንደሚያደርጋት አስረድተዋል።

ይህም የሰለጠነና ብቁ የሰው ኃይል በማፍራት፣ በአፍሪካ የፈጠራ፣ የምርምርና የሰው ኃይል ልማትን የሚያፋጥን ዓለም አቀፍ የልማት አብዮት መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ የትምህርት መሠረተ ልማትን የማስፋፋት ተግባር የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለአፍሪካ አገራት ጭምር በአርአያነት የሚወሰድ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በአንደኛና በቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጤታማነትም ሕፃናትንና ታዳጊዎችን በተሻለ ዕውቀትና ክህሎት በማበልጸግ ሀገር ተረካቢ ዜጋን ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026