የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በደቡብ ወሎ ዞን በበልግ ወቅት ከለማው መሬት ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሐምሌ 14/2018 (ኢዜአ) ፦በደቡብ ወሎ ዞን በበልግ ወቅት የእርሻ ስራ ከለማው መሬት ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ለኢዜአ እንደገለፁት፣ በዞኑ በመኸር፣ በመስኖና በልግ ሰብል ልማት አርሶ አደሩን በንቃት በማሳተፍ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ ጥረት እየተደረገ ነው።

በዚሁ ወቅት ከ104 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ቦሎቄ ፣ ማሾ ፣ ጤፍ ፣ ስንዴ ፣ ሽምብራና ምስር ሰብሎችን ማልማት መቻሉን ገልጸዋል።

ምርታማነቱን ለማሳደግም ግብአትን በአግባቡ በመጠቀምና ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን ተናግረዋል።

በበልግ ሰብል ልማት ከተገኘው ምርት በተጨማሪ ተረፈ ምርቱን ለእንስሳት መኖነት በመጠቀም የወተትና የስጋ ምርትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲጨምር አስችሏል ብለዋል።

የበልግ ዝናቡ ለሰብል ልማት ምቹ እንደነበር አውስተው አሁን ላይ ሰብሉን ቀድሞ በማንሳት ለመኸር ሰብል ልማት ዝግጁ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

በዞኑ አርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ የ07 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር የሱፍ አህመድ እንዳሉት፣ በዘንድሮው የበልግ ዝናብ ከአንድ ሄክታር መሬት በላይ ማሾና ቦሎቄ ማልማት ችለዋል።

ካለሙት መሬት ላይም 12 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን ጠቁመው ከፍጆታ የተረፈውን በመሸጥ ጥሪት ለማፍራት ማቀዳቸውን ተናግረዋል።

ሌላው የተሁለደሬ ወረዳ 013 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ኢብራሂም ደምስ በበኩላቸው፣ በበልግ ዝናብ ካለሙት አንድ ሄክታር መሬት የተሻለ ምርት ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ከእለት ፍጆታ የተረፈውን ምርትም ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026