የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በጋምቤላ ክልል የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Jul 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ ፤ ሐምሌ 16/2018(ኢዜአ)፡- የጋምቤላ ክልልን የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።

የክልሉ አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።


ርዕሰ መስተዳድሯ ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ያጋጠሙ ፈተናዎችን በመቋቋም የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በማዕድን፣ በእንስሳት ሀብት ልማት እንዲሁም በሌሎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የተመዘገቡት ውጤቶች ተስፋ ሰጪ ናቸው ብለዋል።

ከዚሁ ጎን ለጎን በክልሉ የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭን በማስፋት የሕዝቡን ሕይወት ለማሻሻል የተከናወኑ ሥራዎች ውጤታማ እንደነበሩ ጠቁመዋል።

በቀጣይም ዘርፉን ይበልጥ በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ያላሰለሰ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።

በተለይም የክልሉን የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ አበረታች ተግባራት በተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅሰው፣ ወጪ ቆጣቢ የአሰራር ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ለልማትና ለመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተገቢው ምላሽ ይሰጣልም ብለዋል።


የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ ገነት ኤሊያስ በበኩላቸው፤ ቢሮው የልማትና የመልካም አስተዳደር ዕቅዶችን በመንደፍ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ተግባራትን በየደረጃው በመገምገም የተሻለ አፈጻጸም እንዲመዘገብ የማስቻል ሥራ ሲሠራ መቆየቱንም አብራርተዋል።

በዚሁ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የክልሉ የሴክተር መሥሪያ ቤት ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ይጠበቅባቸዋል- ርእሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ነሐሴ 21/2018 (ኢዜአ) ፦ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ...

Aug 28, 2026

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026