የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ የዓባይ ወንዝ ሀብቷን ለማልማት ከማንም ፈቃድ አያስፈልጋትም - የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)

Aug 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የዓባይ ወንዝ ሀብቷን የመጠቀም እና የማልማት ሉዓላዊ መብት ስላላት ከማንም አካል ፈቃድ መጠየቅ እንደማያስፈልጋት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ አክለውም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለቀጣናው የሚተርፍ ሀብት መሆኑንም አመልክተዋል።


ሚኒስትሩ ከፐልስ ኦፍ አፍሪካ (The Pulse of Africa) ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የተገነባው ለኃይል ማመንጨት ብቻ እንደሆነና አዎንታዊ ሚናውን ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ግብይትን በማስፋት ከኢትዮጵያ ድንበር የተሻገረ ጠቀሜታ እንዳለውም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት ማለትም ለጅቡቲ፣ ለኬንያ እና ለሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ላይ እንደምትገኝ የጠቆሙት ሚኒስትሩ፣ ከሶማሊያ እና ከደቡብ ሱዳን በኩል ያለው የኢነርጂ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱንም አብራርተዋል።


የዓባይ ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) እና የዓባይ ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ የወንዙን የጋራ ጥቅም ለማሳደግ የተደረጉ ጥረቶች ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በሌሎች ድንበር ተሻጋሪ የዓለም ወንዞች ላይ ባለው ተሞክሮ ትብብርን የሚጀምሩት የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ቢሆኑም፣ በዓባይ ጉዳይ ግን እንተባበር በማለት ውይይቱን በግንባር ቀደምትነት ስትመራ የቆየችው ኢትዮጵያ መሆኗን አስረድተዋል።

ኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግድብ በታች የሚገኙ ሊለሙ የሚችሉ መሬቶቿን ከመስኖ ልማት ውጪ ማድረጓ ለታችኞቹ የተፋሰሱ ሀገራት ያላትን ትልቅ ግምት እንደሚያሳይ ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።

በቴክኒክ ደረጃ፣ ከግድቡ በታች ከ230 ሺህ ሄክታር በላይ የመስኖ ልማት የሚሆን መሬት አለን፤ ነገር ግን በታችኛው ተፋሰስ በኩል ያለውን ፍላጎት ስለምናውቅ ይህንን አላደረግነውም ሲሉ አስረድተዋል።

ሚኒስትሩ የህዳሴ ግድብ ኃይል ካመነጨ በኋላ የሚለቀቀው ውሃ ቀጥታ ወደ ታችኛው ተፋሰስ ወደሚገኙ ወንድም ሀገራት እንደሚፈስ በመግለጽ ኢትዮጵያ ለጋራ ተጠቃሚነት ያላትን ቁርጠኝነት አንስተዋል።

ሚኒስትሩ ሕዳሴ ግድብን በጋራ ለማስተዳደር የሚቀርቡ ጥሪዎችን ውድቅ ያደረጉ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ሌሎች ሀገራት በግድቡ ላይ ቁጥጥር የሚደረጉበትን አሰራርን አትቀበልም ብለዋል።

በኢትዮጵያውያን ገንዘብ የተገነባውን፣ ኩራታችን እና ብሔራዊ የክብር ፕሮጀክታችን የሆነውን ግድብ፣ ግንባታውን ሲቃወም የነበረ አካል መጥቶ በጋራ እናስተዳድር እንዴት ሊል ይችላል? ሲሉ ጠይቀዋል።

ይህ ፈጽሞ የማይቻል፣ በፍፁም ሊታሰብ የማይችል ነው ሲሉም ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ የዓባይ ተፋሰስ ሀገራት የኢትዮጵያን የልማት መብት ለመገደብ ከመጣር ይልቅ በውይይት እና በትብብር ላይ ትኩረት ማድረግ አለባቸው የሚል የጸና አቋም እንዳላት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026