የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኤአይ፣ የዲጂታል ጤና እና የአረንጓዴ ልማት ራዕይ የሚደነቅ ነው -በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ

Aug 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰው ሠራሽ አስተውሎትን (AI) እና የዲጂታል ጤና ቴክኖሎጂዎችን ከሀገራዊ የልማት እንቅስቃሴዎች ጋር በማቀናጀት እያከናወኑ ያሉትን አርቆ አሳቢነትን የተከተሉ ስራዎች የሚደነቁ መሆናቸውን በዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ፍራንሲስ ቺሳካ ካሶሎ ገለጹ።

ሀገራዊ የልማት እንቅስቃሴዎቹ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን፣የከተሞች ማዘመን እና የወንዞች ዳርቻ ልማት ስራዎችን ያካተቱ ናቸው።

በኢትዮጵያ፣በአፍሪካ ህብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ፍራንሲስ ቺሳካ ካሶሎ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ የማህበረሰብ ጤና ተደራሽነትን በማስፋት ሂደት ውስጥ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ረገድ ግንባር ቀደም ሀገር ናት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአፍሪካ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና አምባሳደር ናቸው፤ በዚህም ከአፍሪካ ህብረት እውቅና እና ሽልማት አግኝተዋል ብለዋል።

ተወካዩ አክለውም በጤናው ዘርፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማስፋፋት በሚደረገው ጥረት የዓለም ጤና ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከጤና ሚኒስቴር ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የአየር ጥራትን ማሻሻል እና ደህንነቱ የተጠበቀ አካባቢን መፍጠር የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን እና የካንሰር ስጋቶችን እንደሚቀንስ በመግለጽ፣ የአካባቢ ጥበቃ ፖሊሲዎች ለህዝብ ጤና ወሳኝ ምሰሶ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ከዚህ አኳያም የኢትዮጵያን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እና የከተማ ልማት ተግባራት ከጤና ጥበቃ እና ቅድመ-መከላከል ስራዎች ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አረንጓዴ አሻራ የአየር ጥራትን ያሻሽላል፤ ንጹህ አየር ደግሞ ለተሻለ ጤንነትና የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ሲሉ አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት የአካባቢ ጽዳትና ንፅህናን በማስጠበቅ ረገድ ያለውን የጤና ጥቅም በአጽንኦት አንስተዋል።

የኮሪደር ልማቱ የአካባቢ ጽዳትን እንደሚያሻሽል የጠቆሙት ተወካዩ፣ ስራው በሀገር አቀፍ ደረጃ መስፋቱ በውሃ ወለድ አምጪ ተህዋሲያን የሚመጡ በሽታዎችን እንደሚቀንስ አመልክተዋል።

መንግስት የከተሞችን ውበት ከማስጠበቅ ባለፈ የአየር ጥራትንና የህዝብን ጤና ለመጠበቅ በአረንጓዴ መሰረተ ልማቶች ላይ እያፈሰሰ ያለው ሀብትና የሰጠው ትኩረት ሊደነቅ የሚገባው ነው ብለዋል።

በአረንጓዴ መሰረተ ልማት እና ጤናማ ከተሞች (healthy cities) እንዲሰፉ የሚያፈሰው መዋዕለ ንዋይ ከተሞችን ከማስዋብ ባሻገር፣ የህዝብን ጤና በዘላቂነት ለመጠበቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ነው የገለጹት።

በዚህ ረገድም መንግስት ትኩረቱን ከህክምና ወጪ ይልቅ በሽታን ወደ መከላከል አቅጣጫ በማዞር በቅድመ-መከላከል ስራዎች ላይ እያከናወነ ያለውን ስራ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል።

በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ተሞክሮ በመላው አፍሪካ ሊደገም እንደሚገባ ተወካዩ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026