የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ኢትዮጵያ በሆርቲካልቸር ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያጎለብት ምቹ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት አቅም አላት - የሕንድ ባለሀብት ጋጄንድራ ሲንግ

Aug 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በአትክልትና ፍራፍሬ የግብርና ልማት ዘርፍ ዓለም አቀፍ የገበያ ተወዳዳሪነትን የሚያጎለብት ምቹ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት አቅም እንዳላት በግብርና ኢንቨስትመንት የተሰማሩት የሕንድ ባለሀብት ጋጄንድራ ሲንግ ገለጹ።

ጋጄንድራ ሲንግ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ቦዲቲ አካባቢ በአቮካዶ ልማት ተሰማርተው እየሰሩ ይገኛሉ።

በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍም በበርካታ ሀገራት የገበያ ጥናት በማካሄድ ለሆርቲካልቸር ዘርፍ ባላት ምቹ የተፈጥሮ ሁኔታና ጠንካራ የመንግሥት ድጋፍ ምክንያት ኢትዮጵያን መምረጣቸውን ተናግረዋል።

በዚህም በኢትዮጵያ የተፈጠረውን ምቹ የግብርና ኢንቨስትመንት ምኅዳር መሰረት ያደረገ የአዋጭነት ጥናት በማካሄድ በፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ተሰማርተው እየሰሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ በተለይም በሆርቲካልቸር ዘርፍ ያላት ከፍተኛ የመልማት አቅም በመጠቀም ባለሀብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን ፈሰስ በማድረግ የሚጠቀሙበት ዕድል የተፈጠረባት ሀገር መሆኗን አንስተዋል።

በኢትዮጵያ ካለው የሀገር ውስጥ ገበያ ባለፈ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ገበያ ምርቶችን ማቅረብ የሚያስችል የልማት ከባቢ መፈጠሩንም አስገንዝበዋል።

መንግሥት በግብርና ዘርፍ ለተሰማሩ አርሶ አደሮች ድጋፍ እያደረገ ነው ያሉት ጋጄንድራ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ለኢንቨስትመንት የሰጠው ቁርጠኝነትም ምቹ የልማት ምኅዳር ፈጥሯል ብለዋል።

በአዲስ አበባ እየተሠራ ያለው ሥራ የከተማዋን ገጽታ ከማሻሻል ባሻገር፤ በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ግዙፍ የአየር ማረፊያ የመንግሥት የልማት ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።

መንግሥት በአቮካዶ ምርት ላይ አበረታች ተግባር እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ በገበያ ተደራሽነት ላይም እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አንስተዋል።

ኢትዮጵያ በቡና ወጪ ንግድ ያላትን ልምድ በመጠቀም በሆርቲካልቸር ዘርፍ ግንባር ቀደም ላኪ የመሆን ዕድል እንዳላት አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢሉባቦር ዞን በኩታ ገጠም ከለማው የበቆሎ ሰብል የተሻለ ምርት ለማገኘት የእንክብካቤ ስራ ተጠናክሯል

መቱ፤ ነሐሴ 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በኢሉባቦር ዞን በክረምት እርሻ እየለማ ከሚገኘው የበቆሎ ሰብል የላቀ ምርት ለማገኘት የሰብል እንክብካቤና ጥ...

Aug 18, 2026

በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

ሀዋሳ፤ ነሐሴ 2/2018 (ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማትን በማሻሻል ለሕዝቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆና...

Aug 10, 2026

በክልሉ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ የልማት ሥራዎች ተከናውነዋል 

አዳማ፤ ሐምሌ 12/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል በበጀት ዓመቱ ሰላምና መልካም አስተዳደርን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ውጤታማ የልማት ሥራዎች መከናወናቸውን የክል...

Jul 20, 2026

የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃት የአካባቢውን የንግድ፣ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያነቃቃ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦የአየር ማረፊያው ለአገልግሎት መብቃትም የአካባቢውን የንግድ፣የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማ...

Jul 13, 2026